የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የጋምቤላ ከተማ የኮሪደር ልማት በጥራትና በፍጥነት እንዲጠናቀቅ ትኩረት ተሰጥቷል - ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ

Jun 24, 2025

IDOPRESS

በጋምቤላ፤ ሰኔ 16/2017(ኢዜአ)፦ የጋምቤላ ከተማ የኮሪደር ልማት በጥራትና በፍጥነት እንዲጠናቀቅ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ ገለፁ።

በጋምቤላ ከተማ የኮሪደር ልማት ግንባታ ላይ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በጋምቤላ ከተማ ተወያይተዋል።።

ርዕሰ መስተዳድሯ በመድረኩ እንዳሉት በክልሉ የኮሪደር ልማት ዘግይቶ ቢጀመርም በጥሩ አፈፃፀም ላይ ይገኛል።

በጋምቤላ ከተማ ለኮሪደር ልማት ስምንት የተመረጡ ቦታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው በመጀመሪያው ምዕራፍ በአራት ዋና ዋና መንገዶች ላይ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።


በጋምቤላ ከተማ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ጥራትና ፍጥነቱን ጠብቆ እንዲጠናቀቅ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

የክልሉ ህዝብም ለኮሪደር ልማቱ ባለው አወንታዊ አመለካከት ለልማቱ ትብብር እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በክልሉ ርዕሰ ከተማ ጋምቤላን ጨምሮ በገጠር ከተሞች ለሚከናወነው የኮሪደር ልማቶች ስኬታማነት ኮሚቴ ተዋቅሮ ሀብት የማሰባሰብ ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልፀዋል።


በከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ካሊድ አብዱረህማን በበኩላቸው በክልሉ የኮሪደር ልማት ዘግይቶ ቢጀመርም አፈፃፀሙ አበረታች መሆኑን አንስተዋል።

የውይይት መድረኩ አላማም በክልሉ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት አፈፃፀም በመገምገም ውስንነቶቹ ላይ ድጋፍ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።


በጋምቤላ ከተማ እየተተገበረ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ሀገር አቀፍ ደረጃውን ጠብቆ መተግበሩን በመከታተልና በመቆጣጠር በኩል ትኩረት ይፈልጋል ብለዋል።

በተለይም የኮሪደር ልማቱ የመብራት፣ የስልክ፣ የውሃና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን አቀናጅቶ ለመተግበር የተጀመረው ስራ ሊጠናከር የሚገባው መሆኑን አንስተዋል።

ከውይይት መድረኩ በኃላ በጋምቤላ ከተማ እየተከናወነ የሚገኘውን የመጀመሪያ ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026