
በጋምቤላ፤ ሰኔ 16/2017(ኢዜአ)፦ የጋምቤላ ከተማ የኮሪደር ልማት በጥራትና በፍጥነት እንዲጠናቀቅ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ ገለፁ።
በጋምቤላ ከተማ የኮሪደር ልማት ግንባታ ላይ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በጋምቤላ ከተማ ተወያይተዋል።።
ርዕሰ መስተዳድሯ በመድረኩ እንዳሉት በክልሉ የኮሪደር ልማት ዘግይቶ ቢጀመርም በጥሩ አፈፃፀም ላይ ይገኛል።
በጋምቤላ ከተማ ለኮሪደር ልማት ስምንት የተመረጡ ቦታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው በመጀመሪያው ምዕራፍ በአራት ዋና ዋና መንገዶች ላይ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በጋምቤላ ከተማ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ጥራትና ፍጥነቱን ጠብቆ እንዲጠናቀቅ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
የክልሉ ህዝብም ለኮሪደር ልማቱ ባለው አወንታዊ አመለካከት ለልማቱ ትብብር እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በክልሉ ርዕሰ ከተማ ጋምቤላን ጨምሮ በገጠር ከተሞች ለሚከናወነው የኮሪደር ልማቶች ስኬታማነት ኮሚቴ ተዋቅሮ ሀብት የማሰባሰብ ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልፀዋል።

በከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ካሊድ አብዱረህማን በበኩላቸው በክልሉ የኮሪደር ልማት ዘግይቶ ቢጀመርም አፈፃፀሙ አበረታች መሆኑን አንስተዋል።
የውይይት መድረኩ አላማም በክልሉ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት አፈፃፀም በመገምገም ውስንነቶቹ ላይ ድጋፍ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።

በጋምቤላ ከተማ እየተተገበረ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ሀገር አቀፍ ደረጃውን ጠብቆ መተግበሩን በመከታተልና በመቆጣጠር በኩል ትኩረት ይፈልጋል ብለዋል።
በተለይም የኮሪደር ልማቱ የመብራት፣ የስልክ፣ የውሃና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን አቀናጅቶ ለመተግበር የተጀመረው ስራ ሊጠናከር የሚገባው መሆኑን አንስተዋል።
ከውይይት መድረኩ በኃላ በጋምቤላ ከተማ እየተከናወነ የሚገኘውን የመጀመሪያ ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026