
በጋምቤላ፤ ሰኔ 16/2017(ኢዜአ)፦ የጋምቤላ ከተማ የኮሪደር ልማት በጥራትና በፍጥነት እንዲጠናቀቅ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ ገለፁ።
በጋምቤላ ከተማ የኮሪደር ልማት ግንባታ ላይ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በጋምቤላ ከተማ ተወያይተዋል።።
ርዕሰ መስተዳድሯ በመድረኩ እንዳሉት በክልሉ የኮሪደር ልማት ዘግይቶ ቢጀመርም በጥሩ አፈፃፀም ላይ ይገኛል።
በጋምቤላ ከተማ ለኮሪደር ልማት ስምንት የተመረጡ ቦታዎች መኖራቸውን ጠቅሰው በመጀመሪያው ምዕራፍ በአራት ዋና ዋና መንገዶች ላይ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በጋምቤላ ከተማ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ጥራትና ፍጥነቱን ጠብቆ እንዲጠናቀቅ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
የክልሉ ህዝብም ለኮሪደር ልማቱ ባለው አወንታዊ አመለካከት ለልማቱ ትብብር እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በክልሉ ርዕሰ ከተማ ጋምቤላን ጨምሮ በገጠር ከተሞች ለሚከናወነው የኮሪደር ልማቶች ስኬታማነት ኮሚቴ ተዋቅሮ ሀብት የማሰባሰብ ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልፀዋል።

በከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ካሊድ አብዱረህማን በበኩላቸው በክልሉ የኮሪደር ልማት ዘግይቶ ቢጀመርም አፈፃፀሙ አበረታች መሆኑን አንስተዋል።
የውይይት መድረኩ አላማም በክልሉ እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት አፈፃፀም በመገምገም ውስንነቶቹ ላይ ድጋፍ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።

በጋምቤላ ከተማ እየተተገበረ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ሀገር አቀፍ ደረጃውን ጠብቆ መተግበሩን በመከታተልና በመቆጣጠር በኩል ትኩረት ይፈልጋል ብለዋል።
በተለይም የኮሪደር ልማቱ የመብራት፣ የስልክ፣ የውሃና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን አቀናጅቶ ለመተግበር የተጀመረው ስራ ሊጠናከር የሚገባው መሆኑን አንስተዋል።
ከውይይት መድረኩ በኃላ በጋምቤላ ከተማ እየተከናወነ የሚገኘውን የመጀመሪያ ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026