
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦ በሁሉም የአገሪቷ አካባቢዎች የተገነቡና የህብረተሰቡን የኑሮ ሁኔታ የሚያሻሽሉ ከ20ሺህ በላይ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብስባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመገኘት የመንግስት የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው።
የምክር ቤቱ አባላት በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ፣ ዲፕሎማሲ እና በሌሎች ጉዳዮች ጥያቄና አስተያየታቸውን አቅርበዋል።
የኮሪደር ልማትን በሚመለከት በሁሉም የአገሪቷ ከተሞች የሚካሄዱ ልማቶች አሳታፊነት ላይ ከምክር ቤቱ ለቀረበላቸው ጥያቄ መንግስት ከኮሪደር በተጨማሪ በርካታ የልማት ስራዎች ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል።
ከዚህ መካከል መንግስት የህብረተሰቡን የኑሮ ሁኔታ የሚያሻሻሉና በማህበረሰቡ ሲጠየቁ የቆዩ መሰረተ ልማቶችን በማሟላት ረገድ በቁርጠኝነት እየሰራ ስለመሆኑም ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት እስከ ነሃሴ መጨረሻ ድረስ የሚመረቁ ከ20 ሺህ በላይ ፕሮጀክቶች መገንባታቸውን ጠቁመዋል።
ፕሮጀክቶቹ የህብረተሰቡን የኑሮ ሁኔታ የሚያሻሽሉ የጤና ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶችና መሰል የመሰረተ ልማት ስራዎች መሆናቸውን አብራርተዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026