
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ)፦ በሁሉም የአገሪቷ አካባቢዎች የተገነቡና የህብረተሰቡን የኑሮ ሁኔታ የሚያሻሽሉ ከ20ሺህ በላይ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 42ኛ መደበኛ ስብስባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመገኘት የመንግስት የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው።
የምክር ቤቱ አባላት በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ፣ ዲፕሎማሲ እና በሌሎች ጉዳዮች ጥያቄና አስተያየታቸውን አቅርበዋል።
የኮሪደር ልማትን በሚመለከት በሁሉም የአገሪቷ ከተሞች የሚካሄዱ ልማቶች አሳታፊነት ላይ ከምክር ቤቱ ለቀረበላቸው ጥያቄ መንግስት ከኮሪደር በተጨማሪ በርካታ የልማት ስራዎች ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል።
ከዚህ መካከል መንግስት የህብረተሰቡን የኑሮ ሁኔታ የሚያሻሻሉና በማህበረሰቡ ሲጠየቁ የቆዩ መሰረተ ልማቶችን በማሟላት ረገድ በቁርጠኝነት እየሰራ ስለመሆኑም ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት እስከ ነሃሴ መጨረሻ ድረስ የሚመረቁ ከ20 ሺህ በላይ ፕሮጀክቶች መገንባታቸውን ጠቁመዋል።
ፕሮጀክቶቹ የህብረተሰቡን የኑሮ ሁኔታ የሚያሻሽሉ የጤና ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶችና መሰል የመሰረተ ልማት ስራዎች መሆናቸውን አብራርተዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026