የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢኮኖሚ ሽግግርን ለማሳለጥ የኢንዱስትሪውን ዘርፍ በጥናትና ምርምር ለማገዝ እየተሠራ ነው

Jul 4, 2025

IDOPRESS

አርባ ምንጭ፤ ሰኔ 26/2017(ኢዜአ) ፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኢኮኖሚ ሽግግርን ለማሳለጥ የኢንዱስትሪውን ዘርፍ በጥናትና ምርምር ለማገዝ እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ።

ክልል አቀፍ የኢንዱስትሪ እምቅ አቅም ልየታ ምርምር ውጤት ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ዛሬ በአርባ ምንጭ ከተማ ተካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ሃላፊ አበባየሁ ታደሰ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር እንዲሳለጥ የኢንዱስትሪ ዘርፍ እምቅ ፀጋዎችን በጥናትና ምርምር ለማገዝ እየተሰራ ነው።


በክልሉ ልማትን ለማረጋገጥ ዘርፉ ያለውን አቅም ለይቶ ለማጠናከር በቅንጅት እንደሚሰራ ጠቅሰው፣ ለዚህም የዘርፉን እምቅ አቅም መለየት ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በኢንዱስትሪ ዘርፍ የሚስተዋሉ የምርታማነት፣ የአቅም እና የድጋፍ አሰጣጥ ማነቆዎችን በመፍታት ሰፊ መደላድል በመፍጠሩ ውጤት እየተመዘገበ ነው ያሉት አበባየሁ (ዶ/ር)፣ በቀጣይም ይህን ማስፋት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

አቅምን ባለማወቅ የኢንዱስትሪ ልማትን በሚፈለገው ልክ ማረጋገጥ እንዳልተቻለ ገልጸው፣ የዘርፉን አቅም በመለየትና ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ለማሳካት በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል።

የክልሉ ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ ቦጋለ ቦሼ (ዶ/ር) በበኩላቸው እንዳሉት በክልሉ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግርን ለማረጋገጥ የኢንዱስትሪ እምቅ ፀጋዎችን ጥቅም ላይ ለማዋል ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።


ባለፉት ሁለት ዓመታት በዘርፉ በተከናወኑ ተግባራት በክልሉ የኢንዱስትሪ ዘርፍ 12 ነጥብ 6 በመቶ ዕድገት መመዝገቡንም ተናግረዋል።

በጥናትና ምርምር ታግዞ ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ተገቢውን ድጋፍ ለማድረግ ከአርባ ምንጭ፣ ከወላይታ ሶዶ፣ ከዲላ እና ጂንካ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ዘርፉን በማዘመንና ምርታማነት በማሳደግ ከተኪና ወጪ ምርቶች የሚገኘውን የውጭ ምንዛሬ በማሳደግ የክልሉንና የሀገርን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ቦጋለ (ዶ/ር) አስታውቀዋል።

የጥናት ውጤቱን ያቀረቡት የክልሉ ፖሊሲ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ በረከት ረጋሳ (ዶ/ር) በተደረገው ጥናት መሠረት በክልሉ የኢንዱስትሪውን እንቅስቃሴ የሚያሳልጡ የተፈጥሮ ጸጋዎችና አምራች ሃይል መኖሩን ገልጸዋል።


በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በማዕድን፣ በኮንስትራክሽንና በቱሪዝም ዘርፍ የክልሉን ኢኮኖሚያዊ መዋቅራዊ ሽግግር የሚያሳልጡ አቅሞች በጥናቱ መዳሰሳቸውን አስረድተዋል።

በዘርፉ ያለውን እምቅ አቅም ለማወቅ የተደረገው ጥናት የክልሉን ኢኮኖሚ ለማፋጠን፣ የህዝብን የነፍስ ወከፍ ገቢ ለማሳደግ እና የሥራ ዕድል ለመፍጠር ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረውም አስገንዝበዋል።

ኢንስቲትዩቱ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር የክልሉን የኢንዱስትሪ ዘርፍ ፀጋዎች፣ ተግዳሮቶችና የመፍትሄ አቅጣጫዎች በማዘጋጀት በቀጣይ በሀገሪቱ እድገት ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ ለማድረግ ይሰራል ብለዋል።

ለአንድ ቀን በተካሄደው መድረክ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የዩኒቨርሲቲ ተወካዮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን የጥናቱን ውጤት ወደ ተግባር መቀየር በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ውይይት ተደርጓል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026