
ሚዛን አማን፣ ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከተሞችን ለሥራና ለኑሮ ምቹ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ የሺዋስ ዓለሙ ገለጹ።
የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ የሺዋስ ዓለሙ እንዳሉት ከተሞችን ለነዋሪው ለሥራና ለኑሮ ምቹ ለማድረግ እየተሰራ ነው።
በዚህም በክልሉ አራት ብዝኃ ዋና ከተሞች ላይ በ450 ሚሊዮን ብር በጀት የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በእስካሁኑም 4 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ስራ ለማከናወን መቻሉን ተናግረዋል።

በኮሪደር ልማት ሥራው የኅብረተሰቡ ሚና የጎላ መሆኑን አንስተው ፕሮጀክቶች በፍጥነት እንዲጠናቀቁና ልማቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠንካራ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ዋና ማዘጋጃ ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ወንድሙ አለማየሁ በከተማዋ በመጀመሪያ ዙር እየተገነባ ያለው 1 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ 95 በመቶ መድረሱን ተናግረዋል።
ስራውን በማስቀጠል በ2018 በጀት ዓመት ከ5 ኪሎ ሜትር በላይ የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ሥራ ለማከናወን መታቀዱንም ጠቅሰዋል።

ኅብረተሰቡ በከተማዋ እየተከናወኑ ላሉ የልማት ሥራዎች ትብብሩን እያሳየ መሆኑንም አመልክተዋል።
ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ጌታሁን ሻዎ እና ወጣት አበበ ሻምፕቴት በመጀመሪያ ዙር የኮሪደር ሥራ በለሙ አረንጓዴ ሥፍራዎች ለመዝናኛ እና አዕምሮን ለማሳረፍ እያገለገሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ልማቱን ይበልጥ በማስፋፋት ለከተማዋ ዕድገት የሚያበርክተውን አስተዋጽኦ ማጉላት እንደሚገባ አክለዋል።


የኮሪደር ልማት የትራፊክ መጨናነቅን ማስቀረት፣ የከተማ ዕድገት ማረጋገጥና ጽዱና ምቹ መኖሪያ አካባቢን መፍጠር ያስችላል ብለዋል።
በቀጣይም ልማቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026