
ሚዛን አማን፣ ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከተሞችን ለሥራና ለኑሮ ምቹ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ የሺዋስ ዓለሙ ገለጹ።
የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ የሺዋስ ዓለሙ እንዳሉት ከተሞችን ለነዋሪው ለሥራና ለኑሮ ምቹ ለማድረግ እየተሰራ ነው።
በዚህም በክልሉ አራት ብዝኃ ዋና ከተሞች ላይ በ450 ሚሊዮን ብር በጀት የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በእስካሁኑም 4 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ስራ ለማከናወን መቻሉን ተናግረዋል።

በኮሪደር ልማት ሥራው የኅብረተሰቡ ሚና የጎላ መሆኑን አንስተው ፕሮጀክቶች በፍጥነት እንዲጠናቀቁና ልማቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠንካራ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ዋና ማዘጋጃ ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ወንድሙ አለማየሁ በከተማዋ በመጀመሪያ ዙር እየተገነባ ያለው 1 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ 95 በመቶ መድረሱን ተናግረዋል።
ስራውን በማስቀጠል በ2018 በጀት ዓመት ከ5 ኪሎ ሜትር በላይ የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ሥራ ለማከናወን መታቀዱንም ጠቅሰዋል።

ኅብረተሰቡ በከተማዋ እየተከናወኑ ላሉ የልማት ሥራዎች ትብብሩን እያሳየ መሆኑንም አመልክተዋል።
ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ጌታሁን ሻዎ እና ወጣት አበበ ሻምፕቴት በመጀመሪያ ዙር የኮሪደር ሥራ በለሙ አረንጓዴ ሥፍራዎች ለመዝናኛ እና አዕምሮን ለማሳረፍ እያገለገሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ልማቱን ይበልጥ በማስፋፋት ለከተማዋ ዕድገት የሚያበርክተውን አስተዋጽኦ ማጉላት እንደሚገባ አክለዋል።


የኮሪደር ልማት የትራፊክ መጨናነቅን ማስቀረት፣ የከተማ ዕድገት ማረጋገጥና ጽዱና ምቹ መኖሪያ አካባቢን መፍጠር ያስችላል ብለዋል።
በቀጣይም ልማቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026