የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከተሞችን ለሥራና ለኑሮ ምቹ ለማድረግ እየተሰራ ነው

Jul 7, 2025

IDOPRESS

ሚዛን አማን፣ ሰኔ 28/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከተሞችን ለሥራና ለኑሮ ምቹ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ የሺዋስ ዓለሙ ገለጹ።

የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ የሺዋስ ዓለሙ እንዳሉት ከተሞችን ለነዋሪው ለሥራና ለኑሮ ምቹ ለማድረግ እየተሰራ ነው።

በዚህም በክልሉ አራት ብዝኃ ዋና ከተሞች ላይ በ450 ሚሊዮን ብር በጀት የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በእስካሁኑም 4 ነጥብ 9 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ስራ ለማከናወን መቻሉን ተናግረዋል።


በኮሪደር ልማት ሥራው የኅብረተሰቡ ሚና የጎላ መሆኑን አንስተው ፕሮጀክቶች በፍጥነት እንዲጠናቀቁና ልማቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠንካራ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ዋና ማዘጋጃ ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ወንድሙ አለማየሁ በከተማዋ በመጀመሪያ ዙር እየተገነባ ያለው 1 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ 95 በመቶ መድረሱን ተናግረዋል።

ስራውን በማስቀጠል በ2018 በጀት ዓመት ከ5 ኪሎ ሜትር በላይ የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ሥራ ለማከናወን መታቀዱንም ጠቅሰዋል።


ኅብረተሰቡ በከተማዋ እየተከናወኑ ላሉ የልማት ሥራዎች ትብብሩን እያሳየ መሆኑንም አመልክተዋል።

ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል አቶ ጌታሁን ሻዎ እና ወጣት አበበ ሻምፕቴት በመጀመሪያ ዙር የኮሪደር ሥራ በለሙ አረንጓዴ ሥፍራዎች ለመዝናኛ እና አዕምሮን ለማሳረፍ እያገለገሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ልማቱን ይበልጥ በማስፋፋት ለከተማዋ ዕድገት የሚያበርክተውን አስተዋጽኦ ማጉላት እንደሚገባ አክለዋል።



የኮሪደር ልማት የትራፊክ መጨናነቅን ማስቀረት፣ የከተማ ዕድገት ማረጋገጥና ጽዱና ምቹ መኖሪያ አካባቢን መፍጠር ያስችላል ብለዋል።

በቀጣይም ልማቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026