
ወልዲያ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ) ፡-የተፈጥሮ ማዳበሪያ አዘጋጅተው መጠቀማቸው የአፈር ለምነትን በማሻሻል ምርታማነትን ከማሳደግ በሻገር ለማዳባሪያ ግዥ ያወጡት የነበረን ገንዘብ ማስቀረቱን በሰሜን ወሎ ዞን አርሶ አደሮች ገለጹ።
የዞኑ ግብርና መምሪያ በበኩሉ ለበልግና ለመኸር እርሻ ልማት ከ4 ነጥብ 9 ሚሊዮን በላይ ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ መዘጋጀቱን አስታውቋል።
በዞኑ ሃብሩ ወረዳ የቁጥር አምስት ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አያሌው አበራ ለኢዜአ እንደገለጹት ባለፉት ሦስት ዓመታት የተፈጥሮ ማዳበሪያ በማዘጋጀት ሦስት ጥማድ መሬታቸውን ሲያለሙ ቆይተዋል።
የተፈጥሮ ማዳበሪያው ለምርታማነት መጨመር ያለውን ፋይዳ በተግባር በማየታቸውም ዘንድሮም 16 ኩንታል ኮምፖስት በማዘጋጀት ለተያዘው የመኸር እርሻ ጥቅም ላይ እያዋሉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በዚህም ዘንድሮ ለዘመናዊ ማዳበሪያ ግዥ ያወጡት የነበረን 17ሺህ 700 ብር ለማዳን መቻላቸውን ገልጸዋል።
በጉባላፍቶ ወረዳ የአማዬ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ደሳለ ጉግሳ በበኩላቸው፣ የተፈጥሮ ማዳበሪያ የአፈር ለምነትን ከማሻሻል በተጨማሪ ወጪን ለመቀነስ እያገዛቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ዘንድሮ ከ14 ኩንታል በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጀታቸውን ጠቁመው፣ በአሁኑ ወቅትም በእርሻ መሬታቸው ላይ ማዳበሪያውን በመበተን የማዋሃድ ሥራ እያከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የተፈጥሮ ማዳበሪያ እርጥበትን አቅቦ በመያዝ ምርታማነትን ለማሳደግ ጉልህ ድርሻ እንዳለው ገልጸው፣ በቀጣይም የተፈጥሮ ማዳበሪያ አዘጋጅተው መጠቀማቸውን እንደሚያጠናክሩ ተናግረዋል።

የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በሰሜን ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ የአፈር ለምነት ማስፋፊያና ማሻሻያ ባለሙያ አቶ ደርቤ አያሌው ናቸው።
ዘንድሮም ከ4 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ፣ 17 ሺህ 934 ሜትር ኪዩብ ባዮ ሳለሪ ኮምፖስት እና 136 ሺህ 582 ኩንታል ቨርሚ ኮምፖስት መዘጋጀቱን ተናግረዋል።
በኮምፖስት ዝግጅቱ 330 ሺህ 638 አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን የገለጹት ባለሙያው፣ የተዘጋጀው የተፈጥሮ ማዳበሪያም 140 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ መሬት በማልማት ምርታማነትን ለማሳደግ እንደሚያስችልም አስረድተዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026