የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የተፈጥሮ ማዳበሪያ የአፈር ለምነትን አሻሽሎልናል፤ከወጪም ታድጎናል-አርሶአደሮች

Jul 8, 2025

IDOPRESS

ወልዲያ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ) ፡-የተፈጥሮ ማዳበሪያ አዘጋጅተው መጠቀማቸው የአፈር ለምነትን በማሻሻል ምርታማነትን ከማሳደግ በሻገር ለማዳባሪያ ግዥ ያወጡት የነበረን ገንዘብ ማስቀረቱን በሰሜን ወሎ ዞን አርሶ አደሮች ገለጹ።

የዞኑ ግብርና መምሪያ በበኩሉ ለበልግና ለመኸር እርሻ ልማት ከ4 ነጥብ 9 ሚሊዮን በላይ ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ መዘጋጀቱን አስታውቋል።

በዞኑ ሃብሩ ወረዳ የቁጥር አምስት ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አያሌው አበራ ለኢዜአ እንደገለጹት ባለፉት ሦስት ዓመታት የተፈጥሮ ማዳበሪያ በማዘጋጀት ሦስት ጥማድ መሬታቸውን ሲያለሙ ቆይተዋል።

የተፈጥሮ ማዳበሪያው ለምርታማነት መጨመር ያለውን ፋይዳ በተግባር በማየታቸውም ዘንድሮም 16 ኩንታል ኮምፖስት በማዘጋጀት ለተያዘው የመኸር እርሻ ጥቅም ላይ እያዋሉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በዚህም ዘንድሮ ለዘመናዊ ማዳበሪያ ግዥ ያወጡት የነበረን 17ሺህ 700 ብር ለማዳን መቻላቸውን ገልጸዋል።

በጉባላፍቶ ወረዳ የአማዬ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ደሳለ ጉግሳ በበኩላቸው፣ የተፈጥሮ ማዳበሪያ የአፈር ለምነትን ከማሻሻል በተጨማሪ ወጪን ለመቀነስ እያገዛቸው መሆኑን ተናግረዋል።

ዘንድሮ ከ14 ኩንታል በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጀታቸውን ጠቁመው፣ በአሁኑ ወቅትም በእርሻ መሬታቸው ላይ ማዳበሪያውን በመበተን የማዋሃድ ሥራ እያከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የተፈጥሮ ማዳበሪያ እርጥበትን አቅቦ በመያዝ ምርታማነትን ለማሳደግ ጉልህ ድርሻ እንዳለው ገልጸው፣ በቀጣይም የተፈጥሮ ማዳበሪያ አዘጋጅተው መጠቀማቸውን እንደሚያጠናክሩ ተናግረዋል።


የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በሰሜን ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ የአፈር ለምነት ማስፋፊያና ማሻሻያ ባለሙያ አቶ ደርቤ አያሌው ናቸው።

ዘንድሮም ከ4 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ፣ 17 ሺህ 934 ሜትር ኪዩብ ባዮ ሳለሪ ኮምፖስት እና 136 ሺህ 582 ኩንታል ቨርሚ ኮምፖስት መዘጋጀቱን ተናግረዋል።

በኮምፖስት ዝግጅቱ 330 ሺህ 638 አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን የገለጹት ባለሙያው፣ የተዘጋጀው የተፈጥሮ ማዳበሪያም 140 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ መሬት በማልማት ምርታማነትን ለማሳደግ እንደሚያስችልም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026