የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የተፈጥሮ ማዳበሪያ የአፈር ለምነትን አሻሽሎልናል፤ከወጪም ታድጎናል-አርሶአደሮች

Jul 8, 2025

IDOPRESS

ወልዲያ፤ ሰኔ 30/2017(ኢዜአ) ፡-የተፈጥሮ ማዳበሪያ አዘጋጅተው መጠቀማቸው የአፈር ለምነትን በማሻሻል ምርታማነትን ከማሳደግ በሻገር ለማዳባሪያ ግዥ ያወጡት የነበረን ገንዘብ ማስቀረቱን በሰሜን ወሎ ዞን አርሶ አደሮች ገለጹ።

የዞኑ ግብርና መምሪያ በበኩሉ ለበልግና ለመኸር እርሻ ልማት ከ4 ነጥብ 9 ሚሊዮን በላይ ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ መዘጋጀቱን አስታውቋል።

በዞኑ ሃብሩ ወረዳ የቁጥር አምስት ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አያሌው አበራ ለኢዜአ እንደገለጹት ባለፉት ሦስት ዓመታት የተፈጥሮ ማዳበሪያ በማዘጋጀት ሦስት ጥማድ መሬታቸውን ሲያለሙ ቆይተዋል።

የተፈጥሮ ማዳበሪያው ለምርታማነት መጨመር ያለውን ፋይዳ በተግባር በማየታቸውም ዘንድሮም 16 ኩንታል ኮምፖስት በማዘጋጀት ለተያዘው የመኸር እርሻ ጥቅም ላይ እያዋሉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በዚህም ዘንድሮ ለዘመናዊ ማዳበሪያ ግዥ ያወጡት የነበረን 17ሺህ 700 ብር ለማዳን መቻላቸውን ገልጸዋል።

በጉባላፍቶ ወረዳ የአማዬ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ደሳለ ጉግሳ በበኩላቸው፣ የተፈጥሮ ማዳበሪያ የአፈር ለምነትን ከማሻሻል በተጨማሪ ወጪን ለመቀነስ እያገዛቸው መሆኑን ተናግረዋል።

ዘንድሮ ከ14 ኩንታል በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጀታቸውን ጠቁመው፣ በአሁኑ ወቅትም በእርሻ መሬታቸው ላይ ማዳበሪያውን በመበተን የማዋሃድ ሥራ እያከናወኑ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የተፈጥሮ ማዳበሪያ እርጥበትን አቅቦ በመያዝ ምርታማነትን ለማሳደግ ጉልህ ድርሻ እንዳለው ገልጸው፣ በቀጣይም የተፈጥሮ ማዳበሪያ አዘጋጅተው መጠቀማቸውን እንደሚያጠናክሩ ተናግረዋል።


የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ ለተፈጥሮ ማዳበሪያ ዝግጅት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በሰሜን ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ የአፈር ለምነት ማስፋፊያና ማሻሻያ ባለሙያ አቶ ደርቤ አያሌው ናቸው።

ዘንድሮም ከ4 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ማዳበሪያ፣ 17 ሺህ 934 ሜትር ኪዩብ ባዮ ሳለሪ ኮምፖስት እና 136 ሺህ 582 ኩንታል ቨርሚ ኮምፖስት መዘጋጀቱን ተናግረዋል።

በኮምፖስት ዝግጅቱ 330 ሺህ 638 አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን የገለጹት ባለሙያው፣ የተዘጋጀው የተፈጥሮ ማዳበሪያም 140 ሺህ ሄክታር የሚጠጋ መሬት በማልማት ምርታማነትን ለማሳደግ እንደሚያስችልም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026