
ደሴ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ) ፡-በደቡብ ወሎ ዞን በ2017 የበጀት ዓመት ከ235 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የመንገድ ግንባታ እና ጥገና ሥራን በማከናወን ለአገልግሎት ምቹ በመደረጉ የሕብረተሰቡን ችግር ማቃለል መቻሉ ተገለጸ።
በበጀት ዓመቱ ለመንገድ ግንባታ እና ጥገና ሥራ ወጪ የተሸፈነው ከመንግስትና ከሕብረተሰቡ በተገኘ ድጋፍ መሆኑን የደቡብ ወሎ ዞን መንገድ መምሪያ አስታውቋል።
የመምሪያው ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ሐሰን፤ በዞኑ የመንገድ ተደራሽነትን በማስፋትና በአገልግሎት ብዛት የተጎዳን በመጠገን ለአገልግሎት ለማብቃት ሲሰራ መቆየቱን ለኢዜአ ተናግረዋል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ 173 ኪሎ ሜትር አዲስ የጠጠር መንገድ ግንባታ እና አንድ ሺህ 266 ኪሎ ሜትር የተጎዳ ነባር መንገድን ለአገልግሎት ማብቃት መቻሉን አስታውቀዋል።

መንገዱ ቀበሌን ከቀበሌ፣ ቀበሌን ከወረዳ፣ ወረዳን ከወረዳ እና ከዞን የሚያገናኙ ናቸው ያሉት ኃላፊው ፤ በተጨማሪ ሁለት ተንጠልጣይ እና አንድ ኮንክሪት ድልድዮችም መገንባታቸውን ጠቁመዋል።
ይህም ለሕብረተሰቡ ጥያቄ ምላሽ በመስጠት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴዎችን ለማነቃቃትም ከፍተኛ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።
ሕብረተሰቡ የአከባቢውን ሰላም በመጠበቅ ከመንግስት ጎን ተሰልፎ በጉልበቱ፣ በሀሳቡና በገንዘቡ ላደረገው ተሳትፎም ምስጋና አቅርበዋል።
በቃሉ ወረዳ የ029 ቀበሌ ነዋሪ አቶ ሁሴን ኢብራሂም በሰጡት አስተያየት፤ ከቀበሌያቸው እስከ አርዲቦ ያለው መንገድ በአገልግሎት ብዛት በመበላሸቱ ተቸግረው እንደቆዩ አስታውሰዋል።
ዘንድሮ በተሻለ ሁኔታ ተጠግኖ ለአገልግሎት ምቹ በመደረጉ ችግራቸው መቃለሉን ተናግረዋል።

የወረባቦ ወረዳ ነዋሪ አቶ ሰይድ ፈንታው በበኩላቸው፤ በአካባቢያቸው የተሽከርካሪ መንገድ ባለመኖሩ ምርታቸውን ለገበያ ለማቅረብና ሕመምተኛን ወደ ህክምና ለመውሰድ አዳጋች ሆናባቸው መቆየቱን አመልክተዋል።
ዘንድሮ አዲስ መንገድ ተሰርቶላቸው ተሽከርካሪም እየመጣ እንደልባቸው መንቀሳቀስ በመጀመራቸው መደሰታቸውን ገልጸው፤ ለመንገዱ ግንባታ በጉልበታቸውና በገንዘባቸው የድርሻቸውን መወጣታቸውንም ተናግረዋል።
በዞኑ በበጀት ዓመቱ ለተከናወነው የመንገድ ግንባታና የጥገና ሥራ በመንግስትና ሕብረተሰቡ ከ235 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉን ከመንገድ መምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026