የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ፎረሙ የአህጉሪቱ ወጣቶችና ሥራ ፈጣሪዎች ያላቸውን ትስስር እንዲያጠናክሩ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል

Jul 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦ የአፍሪካ የሥራ ፈጠራ ፎረም የአህጉሪቱ ወጣቶችና ሥራ ፈጣሪዎች ያላቸውን ትስስር እንዲያጠናክሩ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለፁ።

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሲካሔድ የቆየው የአፍሪካ የሥራ ፈጠራ ፎረም የማጠናቀቂያ መርኃ ግብር እየተካሄደ ነው።


በመርኃ ግብሩ ላይ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በመድረኩ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራች ነው።

በሀገሪቱ ወጣቶች ሥራ ፈጣሪና የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤት መመዝገቡንም ጠቅሰዋል።

በተለይም አማራጭ የሥራ እድሎችን የማስፋት፣ በየዘርፉ የተሻሻሉ ቴክኖሎጂዎችን የማስረፅና ወጣቱ በኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ያለውን ተሳትፎ ማጉላት ዋነኞቹ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

በዚህ ረገድ ላለፉት ሦስት ቀናት ሲካሔድ የቆየው የሥራ ፈጠራ ፎረም የአህጉሪቱ ወጣቶችና ሥራ ፈጣሪዎች ያላቸውን ትስስር እንዲያጠናክሩ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን አስታውቀዋል።

መድረኩ በተለይም የልምድ ልውውጥ በማድረግ ተሞክሯቸውን እንዲጋሩ እና በዘርፉ ለሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች የጋራ መፍትሄ ለማበጀት አስቻይ ሁኔታዎች እንዲፈጠሩ ማድረጉን ገልጸዋል።

ፎረሙ የአፍሪካ ሀገራት በቀጣይ በዘርፉ በጋራ በሚሰሩባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ስምምነት ከማድረግ ባለፈ ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀመጡበት መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል፡፡

አፍሪካ ቀጣይነት ያለው ልማትን እንድታረጋግጥ በኢኮኖሚ፣ በልማትና በመሰረተ ልማት ማስተሳሰር የጋራ ርብርብና ጥረትን የሚጠይቅ ስለመሆኑም አብራርተዋል።

በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ በሥራ እድልና በተለያዩ ዘርፎች ከአህጉሪቱ ሀገራት ጋር ያላትን ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026