
ወላይታ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ብልጽግናን እውን ለማድረግ ለገጠር መንገድ ተደራሽነት ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በወላይታ ዞን ዳሞት ጋሌ ወረዳ ከ36 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባውን 20 ኪሎ ሜትር የገጠር ተደራሽ መንገድ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።

በዚህ ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት ገጠርን ከከተማ የሚያገናኝ መንገድ መገንባት አርሶ አደሩ የግብርና ምርቱን ለገበያ ለማቅረብና የፋብሪካ ሸቀጦችን በቀላሉ ወደ አካባቢው ማስግባት የሚያስችለው ነው።
ይህም የአርሶ አደሩን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያሳድጋል ያሉት አቶ ጥላሁን፣ የክልሉ መንግስት የህዝብን የመንገድ ተደራሽነት ጥያቄ ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አመልክትዋል።
ዛሬ የተመረቀው መንገድ ለእዚህ አንድ ማሳያ መሆኑን ገልጸው፣ ህብረተሰቡ የተገነቡ መንገዶች ለረጅም ጊዜ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ መጠበቅ እንዳለበትም አሳስበዋል።

የመንገዶቹ መገንባት የአርሶ አደሮችን ማህበራዊ ግንኙነት እንደሚያቀላጥፍ የገለጹት ደግሞ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ ናቸው።
የመንገዶቹ መጠናቀቅ የግብርና ውጤቶችን በቀላሉ ወደ ከተማ ለመውሰድ እንዲሁም ነፍሰጡሮችን ጨምሮ ህሙማንን ወደ ጤና ተቋማት በፍጥነት ለማድረስ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል።
የመንገዶቹ ግንባታ በታለመለት የጊዜ ገደብ ውስጥ እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
መንገዱ ከቦዲቲ ከተማ ተነስቶ ቦሎሶ ሶሬ ወረዳን በማቋረጥ ወደ ወላይታ ሶዶ ከተማ ከሚወስድ የአስፖልት መንገድ ጋር እንደሚያገናኝ ተገልጿል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ርዕሰ መስተደድር ጥላሁን ከበደ፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር) እንዲሁም የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026