
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) ለአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ተፈጻሚነት በቁርጠኝነት መስራቱን እንደሚቀጥል የተቋሙ ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ(ዶ/ር) ገለጹ።
47ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት እና 7ኛው የህብረቱ ቀጣናዊማህበረሰቦች የመንፈቅ ዓመት የጋራ የትብብር ስብሰባ በኢኳቶሪያል ጊኒ ማላቦ እየተካሄደ ይገኛል።

በተጓዳኝም ሶስተኛው በአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ትግበራ ላይ ያተኮረ የቀጣናዊ ማህበረሰቦች ኃላፊዎች የጋራ ስብሰባ ተካሂዷል።
ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ማህበረሰቦች የተቀናጀ የመሰረተ ልማት ትስስር፣ የንግድ ልውውጥና የፖሊሲ ተጣጣሚነትን በመፍጠር የአፍሪካን የኢኮኖሚ ትስስር እውን በማድረግ ያላቸው ቁልፍ ሚና በስብሰባው ተነስቷል።
የምስራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግስታት ባለስልጣን(ኢጋድ) ዋና ፀሐፊ ወርቅነህ ገበየሁ(ዶ/ር) በስብሰባውስለ ኢጋድ ቀጣናዊ የመሰረተ ልማት ማስተር ፕላን ያነሱ ሲሆን ማዕቀፉ ከአፍሪካ ነጻ ንግድ ቀጣና እና አጀንዳ 2063 ጋር የሚመጋገብ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢጋድ ለአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራ በቁርጠኝነት መስራቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል መግለጻቸውን ኢዜአ ከተቋሙ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026