የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ስርዓተ ምግብ ምንድን ነው?

Jul 14, 2025

IDOPRESS

ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስርዓተ ምግብ ጉባኤ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።


ዓለም አቀፍ ሁነቱን ኢትዮጵያ እና ጣልያን በጋራ ያዘጋጃሉ።


የስርዓተ ምግብ ሽግግር እና ትራንስፎርሜሽን ጉባኤው የሚያጠነጥንበት አበይት አጀንዳ ነው።


ለመሆኑ ስርዓተ ምግብ ሲባል ምን ማለት ነው? የሚለውን ጉዳይ እንመልከት።


ስርዓተ ምግብ(Food System) የምግብ ማምረት፣ ማቀነባበር፣ ማሰራጨት፣ መጠቀም እና ማስወገድ ውስጥ ያሉ ሂደቶችና ተግባራትን አጠቃሎ የያዘ ሀሳብ ነው።


ህዝብን በመመገብ ውስጥ ሚና ያላቸው ሰዎች፣ ፀጋዎች፣ ተቋማትና መሰረተ ልማቶችን ያካትታል።


የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "ከራዕይ ወደ ተግባር፤ የኢትዮጵያ ዘላቂና አካታች የምግብ ስርዓት ሽግግር ጉዞ" በሚል መሪ ሀሳብ ዓበይት ትኩረቱን በኢትዮጵያ ሥርዓተ ምግብ ላይ ያደረገ ውይይት ሐምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም አካሂዷል።


የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሴ(ዶ/ር) በምግብ ስርዓት ሽግግር ከምርት እስከ ተጠቃሚ ባለው ሰንሰለት ውስጥ ሁሉን አቀፍ ስራ እየተከናወነ መሆኑን አንስተዋል።


በስርዓተ ምግብ ሂደት ውስጥ ካሉ ጉዳዮች አንዱ እንኳን ቢጓደል ሂደቱ ምሉዕ እንደማይሆንም ገልጸዋል።


ምርት እርሻ፣ የአሳ ምርት፣ የከብት እርባታ እና የተለያዩ የምግብ አመራረት አይነቶችን ያካተተ ነው።


ማቀነባበር ጥሬ ምግብን ጥቅም ላይ ወደሚውሉ ምርቶች የመቀየር ሂደት ሲሆን ስርጭት ትራንስፖርት፣ የመጋዘን ክምችትና ገበያ ማድረስን በስሩ ይዟል።


መጠቀም በሚባለው ደረጃ ምግብ መግዛት እና መብላት ነው።


በምግብ እሴት ሰንሰለት ውስጥ የምግብ ጥራትና ብዛት ጥራት መቀነስ፣ የሚጣሉ ትራፊ ምግቦች አስተዳደርና የምግብ ተረፈ ምርቶችን ወደ ተፈጥሮ ማዳበሪያ (ኮምፖስት) መቀየር የመጨረሻው የስርዓተ ምግብ ሂደት መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ።


የኢኮኖሚ ስርዓት፣ ልማዳዊ ድርጊቶች፣ የመንግስት ፖሊሲዎች፣ የከባቢ አየር ሁኔታ እንዲሁም ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን በስርዓተ ምግብ ውስጥ ያላቸው ሚና ወሳኝ ነው።


ስርዓተ ምግብ ሁለንተናዊ እና ሁሉን አቀፍ መሆኑ በኢትዮጵያ ዘላቂና አካታች የምግብ ስርዓት የሽግግር ጉዞ እውን እንዲሆን ትልቅ ጠቀሜታም አለው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026