የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ግብርን በቴሌ ብር መክፈል ጊዜና እንግልትን ከማስቀረት ባለፈ ሀገራዊ ግዴታችንን በወቅቱ ለመወጣት እያገዘን ነው-በሲዳማ ክልል ግብር ከፋዮች

Jul 15, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ ሐምሌ 7/2017 (ኢዜአ)፦ ግብርን በቴሌ ብር መክፈል ጊዜያቸውን ከመቆጠብና እንግልትን ከማስቀረት ባለፈ ሀገራዊ ግዴታቸውን በወቅቱ ለመወጣት እያገዛቸው መሆኑን የሲዳማ ክልል ግብር ከፋዮች ገለጹ።

የሲዳማ ክልል ገቢዎች ባለስልጣን በበኩሉ በሰባት ቀናት ውስጥ በክልሉ ከሚገኙ የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ በቴክኖሎጂ የታገዘ ዘመናዊ አሰራር መዘርጋቱን አስታውቋል።

በሲዳማ ክልል ከሐምሌ 1 ቀን ጀምሮ የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች በቴክኖሎጂ ታግዘው በቴሌ ብር ሃላፊነታቸውን እየተወጡ ሲሆን ዘመናዊ አሰራሩ ጊዜንና እንግልትን ከመቀነስ ባለፈ ግብራቸውን በወቅቱ በመክፈል ሀገራዊ ግዴታቸውን ለመወጣት እያገዛቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል በክልሉ የሀዋሳ ከተማ ነዋሪው ፕሮፌሰር ብርሃኑ ቦርጂ በማማከር አገልግሎት ከሚያገኙት ገቢ የሚጠበቅባቸውን ግብር በቴሌ ብር መክፈላቸው ጊዜያቸውን እንደቆጠበላቸው ገልጸዋል።


ግብርን በወቅቱ መክፈል መንግስት ለሚያከናውነው የልማት ሥራ አጋዥ መሆኑን ጠቁመው፣ የግብር አሰባሰቡ መዘመኑ ግብር ከፋዩ በወቅቱ የሚጠበቅበትን ለመወጣት እያስቻለው መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ ይርጋለም ከተማ የሚኖረት አቶ ምትኩ ጸጋዬ በበኩላቸው በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራር መዘርጋቱ ግብራቸውን በቴሌ ብር ለመክፈልና ጊዜያቸውን ለመቆጠብ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል፡፡


ግብር ለሃገር እድገት የሚኖረው አስተዋጽኦ የጎላ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ምትኩ የሚጠበቅባቸውን ግብር በታማኝነት እንደከፈሉና ሌሎችም ሃላፊነታቸውን በወቅቱ መወጣት እንዳለባቸው ገልጸዋል።

ግብር መክፈል የዜግነት ግዴታና ለልማት የሚደረግ አስተዋጽኦ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በክልሉ የወንዶገነት ከተማ ነዋሪው አቶ ማሞ ቱላ ናቸው።


በሚኖሩበት ከተማ እየተከናወነ ያለው ፈጣን የልማት እንቅስቃሴ ግዴታቸውን በወቅቱ እንዲከፍሉ ያነሳሳቸው መሆኑን ተናግረው፣ "አገልግሎቱ በቴሌ ብር መታገዙ ጊዜን ከመቆጠብ ባለፈ እንግልትን አስቀርቶልኛል" ብለዋል።

የሲዳማ ክልል ገቢዎች ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተርና የደንበኞች አገልግሎት የታክስ አወሳሰንና የገቢ አሰባሰብ ዘርፍ ሃላፊ ወይዘሮ ሙላት ዮሴፍ በበኩላቸው እንዳሉት፣ በክልሉ ከ35ሺህ 816 በላይ የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዮች ይገኛሉ፡፡

ከእነዚህ ግብር ከፋዮችም በሰባት ተከታታይ ቀናት ውስጥ ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደተግባር ተገብቷል ብለዋል።


በክልሉ ከሚገኙ 45 መዋቅሮች በ31ዱ የገቢ አሰባሰብ ሂደቱ በቴሌብር ታግዞ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው፣ ዘመናዊ የግብር አሰባሰብ ሥርአት መዘርጋቱ ለግብር ከፋዮች ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት ከማስቻሉ ባለፈ ህገወጥ ተግባራትን ለመከላከል እያገዘ ነው ብለዋል።

በተጨማሪም የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመዘርጋት ግብር ከፋዮች ንግድ ፈቃዳቸውን የሚያድሱበት እንዲሁም ሌሎች ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶችን የሚያገኙበት አሰራር መዘርጋቱ እንግልት ያስቀረ፣ ጊዜና ጉልበት የቆጠበ ነው ሲሉም ምክትል ዳይሬክተሯ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026