
አሶሳ፤ሐምሌ 12/2017 (ኢዜአ)፦ በ2018 በጀት ዓመት የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት እንደሚከናወኑ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ።
ለሁለት ቀናት በአሶሳ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የክልሉ የ2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ የ2018 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ተጠናቋል።

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን፤ በ2017 በጀት ዓመት የተከናወኑ የልማት ስራዎችን በተሻለ አፈጻጸም በማስቀጠል በ2018 በጀት ዓመት ተጨባጭ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ይሰራል ብለዋል።
በክልሉ የገቢ አማራጭችን በማስፋት እና የአሰባሰብ ስርዓቱን በማዘመን የመንግሥትን የልማት ወጪ ፍላጎት ለመሸፈን የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
የገቢ አሰባሰብ ላይ የታየው መሻሻል የልማት ስራዎችን ለማከናወን ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር ነው ያሉት አቶ አሻድሊ ባለሃብቶችን እና ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን መታቀዱን ገልጸዋል።
በአሶሳ ከተማ የተጀመረውን የኮሪደር ልማት ወደ ሌሎች ከተሞች በማስፋት፣ የክልሉን የተፈጥሮ ሀብት በማልማት እና በመጠቀም የክልሉን ኢኮኖሚያዊ አቅም ማሳደግ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
የ2018 በጀት ዓመት እንደ ሀገር ትልልቅ ፕሮጀክቶች ወደ ስራ የሚገቡበት መሆኑን ገልፀው ይህም ሀገራዊ ብልጽግና የሚረጋገጥበት መልካም አጋጣሚ እንደሚሆንም ተናግረዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር በበኩላቸው ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን የተጀመሩ ተግባራትን በሁሉም ወረዳዎች የማስፋት ሥራው ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አመላክተዋል።
አመራሩ የተያዙ ዕቅዶችን ከግብ ለማድረስ በቁርጠኝነት ለመስራት ራሱን ዝግጁ ማድረግ እንዳለበትም አቶ ኢሳቅ አሳስበዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026