የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በ2018 በጀት ዓመት የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ይከናወናሉ-አቶ አሻድሊ ሀሰን

Jul 21, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ሐምሌ 12/2017 (ኢዜአ)፦ በ2018 በጀት ዓመት የክልሉን ህዝብ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት እንደሚከናወኑ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ።

ለሁለት ቀናት በአሶሳ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የክልሉ የ2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ የ2018 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ተጠናቋል።


በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን፤ በ2017 በጀት ዓመት የተከናወኑ የልማት ስራዎችን በተሻለ አፈጻጸም በማስቀጠል በ2018 በጀት ዓመት ተጨባጭ ውጤቶችን ለማስመዝገብ ይሰራል ብለዋል።

በክልሉ የገቢ አማራጭችን በማስፋት እና የአሰባሰብ ስርዓቱን በማዘመን የመንግሥትን የልማት ወጪ ፍላጎት ለመሸፈን የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

የገቢ አሰባሰብ ላይ የታየው መሻሻል የልማት ስራዎችን ለማከናወን ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር ነው ያሉት አቶ አሻድሊ ባለሃብቶችን እና ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን መታቀዱን ገልጸዋል።

በአሶሳ ከተማ የተጀመረውን የኮሪደር ልማት ወደ ሌሎች ከተሞች በማስፋት፣ የክልሉን የተፈጥሮ ሀብት በማልማት እና በመጠቀም የክልሉን ኢኮኖሚያዊ አቅም ማሳደግ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የ2018 በጀት ዓመት እንደ ሀገር ትልልቅ ፕሮጀክቶች ወደ ስራ የሚገቡበት መሆኑን ገልፀው ይህም ሀገራዊ ብልጽግና የሚረጋገጥበት መልካም አጋጣሚ እንደሚሆንም ተናግረዋል።


በብልጽግና ፓርቲ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢሳቅ አብዱልቃድር በበኩላቸው ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን የተጀመሩ ተግባራትን በሁሉም ወረዳዎች የማስፋት ሥራው ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አመላክተዋል።



አመራሩ የተያዙ ዕቅዶችን ከግብ ለማድረስ በቁርጠኝነት ለመስራት ራሱን ዝግጁ ማድረግ እንዳለበትም አቶ ኢሳቅ አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026