የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በምዕራብ ሸዋ ዞን ከ18 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነቡ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት ክፍት ሆኑ

Jul 22, 2025

IDOPRESS

አምቦ፤ ሐምሌ 14/ 2017 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ሸዋ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ18 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ 1 ሺህ 500 የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት ክፍት መሆናቸውን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ።

በዞኑ ኤጄሬ ወረዳ የተገነቡ የዲጂታል ፓርክ፣ የማህበረሰብ መድኃኒት ቤት እና የወረዳው የኦሮሚያ ልማት ማህበር ጽህፈት ቤት ህንጻ እና ሌሎች የመሰረተ ልማት ተቋማት ተመርቀዋል።


በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አበበ ጨመዳ እንደገለጹት በዞኑ በህዝብ እና በመንግስት ተሳትፎ የተገነቡ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች በሁሉት ዙር እየተመረቁ ነው።

በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ18 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ግንባታቸው የተከናወኑ 1 ሺህ 500 የተለያዩ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት በቅተዋል።


ለአገልግሎት ከበቁት ፕሮጀክቶች መካከል የትምህርት፣ የጤናና የንጹህ መጠጥ ውሃ ተቋማት እንዲሁም የመንገድ ግንባታ እና ሌሎችም ይገኙበታል ብለዋል።

ፕሮጀክቶቹም የህዝቡን የቆየ የልማት ጥያቄዎች ለመፍታት የተገነቡ መሆኑን ገልጸው ህብረተሰቡም ፕሮጀክቶቹን መጠበቅና መንከባከብ እንዳለበትም አሳስበዋል።

የኤጄሬ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አዱኛ ብሩ በበኩላቸው በወረዳው ለአገልግሎት ከበቁ የልማት ፕሮጀክቶች መካከል የወተት ላሞች እርባታና ከብት ማደለቢያ ማዕከላት፣ የመንገድ መብራት፤ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ ዘመናዊ ቤተ-መጻህፍት፣ የጤና ጣቢያና የመንገድ ግንባታን ያካተተ መሆኑን ገልጸዋል።


በወረዳው በአጠቃላይ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው የመሰረተ ልማት ተቋማት ለአገልግሎት በቅተዋል ብለዋል።

ኢዜአ ያነጋገራቸው በዞኑ የኤጄሬ ወረዳ ነዋሪዎችም በአካባቢያቸው ለአገልግሎት የበቁ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የረጅም ጊዜ ጥያቄያቸውን የሚመልሱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ወይዘሮ ባዳቱ ጫካ እንዳሉት አሁን ላይ በቀበሌያቸው የተገነባው ጤና ጣቢያ አገልግሎት መስጠት በመጀመሩ የህክምና አገልግሎት ለማግኘት ረጅም ርቀት ከመጓዝ እንደታደጋቸው ተናግረዋል።


ሌላኛው የወረዳው ነዋሪ አቶ ጥላሁን ቲክሴ በበኩላቸው፤ በተለይ በክረምት ወቅት ከባድ የመንገድ ችግር እንደነበረ ጠቅሰው አሁን ላይ የተገነባው መንገድ በአካባቢው የማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዲጠናከር የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል።


የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026