የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በደቡብ ወሎ ዞን 57 የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ተደረጉ

Jul 24, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤ ሀምሌ 16/2017 (ኢዜአ)፡-በደቡብ ወሎ ዞን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 57 የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ተጠናቆ ለመጪው በጋ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ መደረጋቸውን የዞኑ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት መምሪያ አስታወቀ።

ከ57ቱ የመስኖ ፕሮጀክቶች ውስጥ 43ቱ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ግንባታቸው ተጀምሮ የተጠናቀቁ መሆናቸውም ተጠቁሟል።


የመምሪያው ኃላፊ አቶ ተክሉ ጥላሁን ለኢዜአ እንደገለፁት በዞኑ የውሃ አማራጮችን በመጠቀም አርሶ አደሩ ምርታማነቱን ማሳደግ እንዲችል የመስኖ ፕሮጀክት ግንባታው ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በ972 ሚሊዮን ብር 57 የመስኖ ፕሮጀክቶችን በማስገንባት ለመጪው የበጋ መስኖ ልማት ዝግጁ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።

ከፕሮጀክቶቹ ውስጥም 43ቱ በ2017 በጀት ዓመት ግንባታቸው ተጀምሮ በበጀት ዓመቱ የተጠናቀቁ ሲሆን ቀሪዎቹ ባለፉት ዓመታት የተጀመሩ እንደነበሩ አስታውሰዋል።


የተገነቡት ፕሮጀክቶችም ከ6 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከ11 ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን በመስኖ ልማት ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚችሉም ተናግረዋል።

በዞኑ በዓመት እስከ ሶስት ጊዜ በማምረት የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥና ገበያውን ከማረጋጋት ባለፈ ከተረጂነት ለመውጣት የሚደረገውን ጥረት የሚደግፉ ናቸው ብለዋል።

የመስኖ ፕሮጀክቶቹ ግንባታ ከተከናወነባቸው መካከል ደሴ ዙሪያ ወረዳ፣ አልብኮ፣ ቦረና፣ መቅደላ፣ ተንታ፣ ለገሂዳና ሌሎች ወረዳዎች እንደሚገኙበትም ጠቅሰዋል።

አርሶ አደሩም ፕሮጀክቶቹን በመጠበቅና በመንከባከብ ለረጅም ጊዜ አገልግሎት እንዲሰጡ በማድረግ ዘላቂ ተጠቃሚነቱን እንዲያሳድግ አሳስበዋል።

በደሴ ዙሪያ ወረዳ የቀበሌ 40 ነዋሪ አርሶ አደር ሰይድ አራጋው በበኩላቸው ዘንድሮ በተገነባላቸው የመስኖ ፕሮጀክት አንድ ሄክታር የሚጠጋ መሬታቸውን በበጋ ስንዴና በቋሚ ፍራፍሬ ለማልማት ተዘጋጅተዋል።


ቀደም ሲል በባህላዊ መስኖ አትክልት ለማልማት ቢሞክሩም ተጠቃሚ መሆን ሳይችሉ መቅረታቸውን ጠቁመው የዘመናዊ መስኖ መገንባቱ ዘላቂ ተጠቃሚነታቸውን እንደሚያረጋግጥላቸውም ተናግረዋል።

ሌላው የመቅደላ ወረዳ 04 ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር አብዱራህማን የሱፍ በሰጡት አስተያየት ዘንድሮ በተገነባላቸው የመስኖ ፕሮጀክት ግማሽ ሄክታር ማሳቸውን በበጋ ስንዴ ለማልማት ተዘጋጅተዋል።


መንግስት የዓመት ዝናብን ሳንጠብቅ በዘመናዊ መስኖ ምርታማነታችንን በማሳደግ ተጠቃሚ መሆን እንድንችል ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩም እናመሰግናለን ብለዋል።

በደቡብ ወሎ ዞን በ2016 በጀት ዓመት በተገነቡ 18 የመስኖ ፕሮጀክቶች ከ3 ሺህ የሚበልጡ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉንም ከመምሪያው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026