
ወልዲያ፤ ሐምሌ 16/2017(ኢዜአ)፡-በፍራፍሬ ልማት መሠማራታቸው ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደገው መምጣቱን የሰሜን ወሎ ዞን አርሶ አደሮች ገለጹ።
የዞኑ ግብርና መምሪያ በበኩሉ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ317 ሺህ ኩንታል በላይ የፍራፍሬ ምርት ለገበያ በማቅረብ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ማድረግ እንደታቸለ አስታውቋል።

በሰሜን ወሎ ዞን ሃብሩ ወረዳ ቡሆሮ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ተገኘ ወርቁ ለኢዜአ እንደገለጹት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከማንጎና ፓፓያ ምርት ሽያጭ ከ87 ሺህ ብር በላይ አግኝተዋል።
በአሁኑ ወቅትም ተጨማሪ የማንጎና ፓፓያ ምርቶችን ለገበያ ማቅረባቸውን ገልጸው፣ በቀጣይም ልማቱን በማስፋፋተ በሚያገኙት ገቢ ወደንግድ ስራ ለመሰማራት ማቀደቻውን ተናግረዋል።
በዞኑ ጉባላፍቶ ወረዳ የአላውሃ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ጎበዜ በላይ በበኩላቸው የማንጎ፣ ፓፓያና ሙዝ ምርት ለገበያ በማቅረብ በበጀት ዓመቱ ከ45 ሺህ ብር በላይ ገቢ መግኘታቸውን ተናግረዋል።
ከፍራፍሬ ልማቱ በሚያገኙት ገቢ ቤተሰባቸውን ከማስተዳደር ባለፈ የኢኮኖሚ አቅማቸው እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።

በሰሜን ወሎ ዞን በመስኖና በመደበኛ እርሻ በ1ሺህ 655 ሄክታር መሬት ላይ ፍራፍሬ መልማቱን የገለጹት ደግሞ በሰሜን ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ የአትክልትና ፍራፍሬ ቡድን መሪ አቶ አለባቸው መራዊ ናቸው።
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመስኖ ከለማው ፍራፍሬ 317 ሺህ 220 ኩንታል ምርት ለገበያ በማቅረብ አርሶ አደሩን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል።
በልማቱም 82 ሺህ 750 አርሶ አደሮች በመሳተፍ ማንጎ፣ አቡካዶ፣ ፓፓያ፣ ሙዝ፣ አፕል፣ ብርቱካንና ሌሎች ፍራፍሬዎችን በመስኖ ማልማታቸውን ተናግረዋል።
አርሶ አደሮቹ ምርታማነታቸውን ለማሳደግ የግብርና ቴክኖሎጂ ከመጠቀም በተጨማሪ የተሻሻሉ የፍራፍሬ ዝርያዎችን እያለሙ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
ከመምሪያው የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው በ2016 በጀት ዓመት በዞኑ ከ310 ሺህ ኩንታል በላይ የፍራፍሬ ምርት ለገበያ በማቅረብ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ተችሏል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026