የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የሰሜን ወሎ ዞን አርሶ አደሮች በፍራፍሬ ልማት መሠማራታቸው ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደገው ነው

Jul 24, 2025

IDOPRESS

ወልዲያ፤ ሐምሌ 16/2017(ኢዜአ)፡-በፍራፍሬ ልማት መሠማራታቸው ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደገው መምጣቱን የሰሜን ወሎ ዞን አርሶ አደሮች ገለጹ።

የዞኑ ግብርና መምሪያ በበኩሉ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ317 ሺህ ኩንታል በላይ የፍራፍሬ ምርት ለገበያ በማቅረብ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ማድረግ እንደታቸለ አስታውቋል።


በሰሜን ወሎ ዞን ሃብሩ ወረዳ ቡሆሮ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ተገኘ ወርቁ ለኢዜአ እንደገለጹት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከማንጎና ፓፓያ ምርት ሽያጭ ከ87 ሺህ ብር በላይ አግኝተዋል።

በአሁኑ ወቅትም ተጨማሪ የማንጎና ፓፓያ ምርቶችን ለገበያ ማቅረባቸውን ገልጸው፣ በቀጣይም ልማቱን በማስፋፋተ በሚያገኙት ገቢ ወደንግድ ስራ ለመሰማራት ማቀደቻውን ተናግረዋል።

በዞኑ ጉባላፍቶ ወረዳ የአላውሃ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ጎበዜ በላይ በበኩላቸው የማንጎ፣ ፓፓያና ሙዝ ምርት ለገበያ በማቅረብ በበጀት ዓመቱ ከ45 ሺህ ብር በላይ ገቢ መግኘታቸውን ተናግረዋል።

ከፍራፍሬ ልማቱ በሚያገኙት ገቢ ቤተሰባቸውን ከማስተዳደር ባለፈ የኢኮኖሚ አቅማቸው እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።


በሰሜን ወሎ ዞን በመስኖና በመደበኛ እርሻ በ1ሺህ 655 ሄክታር መሬት ላይ ፍራፍሬ መልማቱን የገለጹት ደግሞ በሰሜን ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ የአትክልትና ፍራፍሬ ቡድን መሪ አቶ አለባቸው መራዊ ናቸው።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በመስኖ ከለማው ፍራፍሬ 317 ሺህ 220 ኩንታል ምርት ለገበያ በማቅረብ አርሶ አደሩን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አስረድተዋል።

በልማቱም 82 ሺህ 750 አርሶ አደሮች በመሳተፍ ማንጎ፣ አቡካዶ፣ ፓፓያ፣ ሙዝ፣ አፕል፣ ብርቱካንና ሌሎች ፍራፍሬዎችን በመስኖ ማልማታቸውን ተናግረዋል።

አርሶ አደሮቹ ምርታማነታቸውን ለማሳደግ የግብርና ቴክኖሎጂ ከመጠቀም በተጨማሪ የተሻሻሉ የፍራፍሬ ዝርያዎችን እያለሙ መሆናቸውንም ገልጸዋል።

ከመምሪያው የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው በ2016 በጀት ዓመት በዞኑ ከ310 ሺህ ኩንታል በላይ የፍራፍሬ ምርት ለገበያ በማቅረብ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ተችሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026