
ወልቂጤ፤ ሐምሌ 17/2017(ኢዜአ)፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ለ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈጸሚያ የሚውል ከ43 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አጽድቋል።
የክልሉ ምክር ቤት በጀቱን ያጸደቀው በወልቂጤ ከተማ እያካሄደ በሚገኘው 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት 4ኛው መደበኛ ጉባኤ ነው።
በክልሉ ምክር ቤት የፋይናንስና በጀት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ታመነ ገብሬ የተያዘውን በጀት ለወሳኝ ተቋማት እና እንደሀገር በኢኒሼቲቭ ለሚሰሩ ሥራዎች በአግባቡ እንዲውል ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

እንደ አቶ ታመነ ገለጻ በጀቱ በዋናነት ለጤና፣ ለትምህርት፣ ለድህነት ቅነሳ ሥራዎች፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራና ለሌሎች አገልግሎቶች እንደሚውልም ተናግረዋል።
የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ዘይቱና ኢብራሂም በሰጡት ማብራሪያ የበጀቱ ምንጭ የክልሉ የውስጥ ገቢ፣ ከፌደራል መንግስት የሚሰጥ ድጎማ እና ሌሎች የገቢ ምንጮች መሆናቸውን ገልጸዋል።

የዘንድሮ በጀት ከአምናው ጋር ሲነፃፀር የ15 በመቶ እድገት እንዳለው ጠቅሰው፣ ከአጠቃላይ በጀቱ 23 ቢሊዮን 724 ሚሊዮን 463 ብር በክልሉ የውስጥ ገቢ የሚሸፈን ይሆናል ብለዋል።
በራስ አቅም የሚሰበሰብ ገቢ እያደገ በመሆኑ ሁሉም መዋቅሮች የገቢ አሰባሰብ አቅማቸውን ለማሳደግ፣ በጀታቸውን በአግባቡ ለማስተዳደርና ግልጽነት መፍጠር ላይ ትኩረት እንዲሰጡ ኃላፊዋ አሳስበዋል።

የምክር ቤቱ አባላት በቀረበው የበጀት ረቂቅ ላይ ሀሳብና አስተያየት ሰጥተው ከተወያዩ በኋላ በጀቱን አጽድቀዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026