
ወልቂጤ፤ ሐምሌ 17/2017(ኢዜአ)፦ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ለ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ማስፈጸሚያ የሚውል ከ43 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አጽድቋል።
የክልሉ ምክር ቤት በጀቱን ያጸደቀው በወልቂጤ ከተማ እያካሄደ በሚገኘው 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት 4ኛው መደበኛ ጉባኤ ነው።
በክልሉ ምክር ቤት የፋይናንስና በጀት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ታመነ ገብሬ የተያዘውን በጀት ለወሳኝ ተቋማት እና እንደሀገር በኢኒሼቲቭ ለሚሰሩ ሥራዎች በአግባቡ እንዲውል ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

እንደ አቶ ታመነ ገለጻ በጀቱ በዋናነት ለጤና፣ ለትምህርት፣ ለድህነት ቅነሳ ሥራዎች፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራና ለሌሎች አገልግሎቶች እንደሚውልም ተናግረዋል።
የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ዘይቱና ኢብራሂም በሰጡት ማብራሪያ የበጀቱ ምንጭ የክልሉ የውስጥ ገቢ፣ ከፌደራል መንግስት የሚሰጥ ድጎማ እና ሌሎች የገቢ ምንጮች መሆናቸውን ገልጸዋል።

የዘንድሮ በጀት ከአምናው ጋር ሲነፃፀር የ15 በመቶ እድገት እንዳለው ጠቅሰው፣ ከአጠቃላይ በጀቱ 23 ቢሊዮን 724 ሚሊዮን 463 ብር በክልሉ የውስጥ ገቢ የሚሸፈን ይሆናል ብለዋል።
በራስ አቅም የሚሰበሰብ ገቢ እያደገ በመሆኑ ሁሉም መዋቅሮች የገቢ አሰባሰብ አቅማቸውን ለማሳደግ፣ በጀታቸውን በአግባቡ ለማስተዳደርና ግልጽነት መፍጠር ላይ ትኩረት እንዲሰጡ ኃላፊዋ አሳስበዋል።

የምክር ቤቱ አባላት በቀረበው የበጀት ረቂቅ ላይ ሀሳብና አስተያየት ሰጥተው ከተወያዩ በኋላ በጀቱን አጽድቀዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026