የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ከ900 በላይ የመንግስት አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ማድረግ ተችሏል

Jul 30, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 19/2017(ኢዜአ)፦ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ከ900 በላይ የመንግስት አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ማድረግ መቻሉን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የዲጂታል ኢኮኖሚ ዘርፍ መሪ ስራ አስፈፃሚ ስዩም መንገሻ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን እውን ለማድረግ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡

ስትራቴጂው ተግባራዊ መሆን ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በተለያዩ ዘርፎች በርካታ ለውጦች መመዝገባቸውን መሪ ስራ አስፈጻሚው ጠቅሰዋል፡፡

የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት በመዘርጋት፣ የዲጂታል አገልግሎት በማስፋት እንዲሁም ብሔራዊ መታወቂያ ተደራሽ በማድረግ በኩል አመርቂ ሥራዎች መሰራታቸውን ለአብነት አንስተዋል።

በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የዳታ ማዕከላት መገንባታቸውን እንዲሁም የኢንተርኔትና ኤሌክትሪክ አቅርቦት እየተስፋፋ መምጣቱን አብራርተዋል።

በተጨማሪም የሞባይልና የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር በከፍተኛ መጠን መጨመሩንና የዲጂታል የክፍያ ሥርዓት እመርታ እያስመዘገበ መሆኑንም ገልጸዋል።

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ የ2017 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸምን በገለጹበት ወቅት 16 ከተሞችን በ5 ጂ እና 512 ከተሞችን በ4ጂ ኔትወርክ ተደራሽ ማድረግ መቻሉን መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

በርካታ የሞባይል ጣቢያዎች መገንባታቸውን በማንሳት፥ በአሁኑ ወቅት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ10ሺህ በላይ የሞባይል ጣቢያዎች አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙ ገልጸው፤ የአገልግሎት ተጠቃሚዎቹን ቁጥር 83 ነጥብ 2 ሚሊዮን ማድረስ መቻሉን መግለጻቸውም እንዲሁ።

እስካሁን በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ከ900 በላይ የመንግስት አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ማድረግ መቻሉን በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የዲጂታል ኢኮኖሚ ዘርፍ መሪ ስራ አስፈፃሚ ስዩም መንገሻ ገልጸዋል፡፡

የመንግስት አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ማድረግ የሚሰጡ አገልግሎቶችን እንደሚያሳልጥ አንስተው የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለተጠቃሚዎች ተደራሽ እያደረገ ያለውን ውጤታማ አገልግሎት ለአብነት አንስተዋል፡፡


የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መሰረት መስቀሌ በበኩላቸው፤ የመንግሥት ግዥና አስተዳደር ሥርዓትን ዲጂታላይዝ የማድረግ ተግባር ማከናወኑን ገልፀዋል።

በዚህ አገልግሎት አሰጣጡን ፈጣንና ቀልጣፋ በማድረግ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ህግና ፖሊሲ ክፍል ባለሙያ ገብርኤላ አብርሃም፤ ለዲጂታል ኢትዮጵያ ግንባታ አስቻይ ሁኔታ ከሚፈጥሩ ጉዳዮች መካከል አንዱ የብሔራዊ መታወቂያ አገልግሎት መሆኑን ገልጸዋል።

ይህ የአሰራር ስርዓት ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ጊዜ ጀምሮ በህገ ወጥ መልኩ ሲዘጋጁ የነበሩና ወረቀትን መሰረት ያደረጉ አሰራሮችን ማስቀረት መቻሉን አብራርተዋል።

ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ከ20 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለብሔራዊ መታወቂያ መመዝገባቸው ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026