
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 22/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የምግብ ስርዓት ሽግግርንና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ቁርጠኛ ሆና እንደምትቀጥል ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ ገለጹ።
ላለፉት ሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው ሁለተኛው የምግብ ስርዓት ጉባኤ የማጠናቀቂያ መርሀ ግብር በመካሄድ ላይ ነው።
በመድረኩ የኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ታዬ አጽቀስላሴ፣ የጣሊያን መንግስት የምግብ ዋስትና ልዩ መልዕክተኛ ስቴፋኖ ጋቲ እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ምክትል ዋና ጸሀፊ አሚና መሀመድ እና ሌሎች የዓለም ዐቀፍ ተቋማት መሪዎች ተገኝተዋል።
የኢፌድሪ ፕሬዝደንት ታዬ አጽቀስላሴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ጉባኤው የተካሄደው አለም በፈታኝ ሁኔታ ባለችበት ወቅት ነው።
ሀገራት ዘላቂ የሆነ የምግብ ስርዓት ለመገንባት ትኩረት መስጠት እንዳለባቸው ገልጸው፤ የምግብ ስርዓት አጀንዳ የሁላችንም ጉዳይ መሆን አለበት ብለዋል።
የምግብ ስርዓትን ለማረጋገጥ ለእውነተኛ የተግባር ስራ በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ሀገራት ሀብታቸውን አንድ ላይ በማሰባሰብ ስትራቴጂዎችን መትከል እንዳለባቸውም አመላክተዋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በገንዘብና መድረኮችን በመፍጠር እያጋጠሙ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት እየደረጋቸው ያሉ ጥረቶች የሚመሰገኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የምግብ ስርዓትን ለማረጋገጥ ሀገራት ተግባራዊ ምላሽ በመስጠት በቁርጠኝነት መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
እንቅፋቶችን በዘላቂነት ለመፍታት ምክንያት ተኮር ጥረቶች እንዲሁም ውጤታማ ህዝባዊ ንቅናቄን ማድረግ እንደሚገባ ነው ያመላከቱት።
ኢትዮጵያ ይህን አጀንዳ ለመደገፍ ከመቼውም ጊዜ በላይ ቁርጠኛ ሆና እንደምትቀጥልም ገልጸዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026