የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ኢትዮጵያ የምግብ ስርዓት ሽግግርንና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ቁርጠኛነቷን ታጠናክራለች - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ

Jul 30, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 22/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የምግብ ስርዓት ሽግግርንና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ቁርጠኛ ሆና እንደምትቀጥል ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ ገለጹ።

ላለፉት ሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው ሁለተኛው የምግብ ስርዓት ጉባኤ የማጠናቀቂያ መርሀ ግብር በመካሄድ ላይ ነው።

በመድረኩ የኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ታዬ አጽቀስላሴ፣ የጣሊያን መንግስት የምግብ ዋስትና ልዩ መልዕክተኛ ስቴፋኖ ጋቲ እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ምክትል ዋና ጸሀፊ አሚና መሀመድ እና ሌሎች የዓለም ዐቀፍ ተቋማት መሪዎች ተገኝተዋል።

የኢፌድሪ ፕሬዝደንት ታዬ አጽቀስላሴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ጉባኤው የተካሄደው አለም በፈታኝ ሁኔታ ባለችበት ወቅት ነው።

ሀገራት ዘላቂ የሆነ የምግብ ስርዓት ለመገንባት ትኩረት መስጠት እንዳለባቸው ገልጸው፤ የምግብ ስርዓት አጀንዳ የሁላችንም ጉዳይ መሆን አለበት ብለዋል።

የምግብ ስርዓትን ለማረጋገጥ ለእውነተኛ የተግባር ስራ በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ሀገራት ሀብታቸውን አንድ ላይ በማሰባሰብ ስትራቴጂዎችን መትከል እንዳለባቸውም አመላክተዋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በገንዘብና መድረኮችን በመፍጠር እያጋጠሙ ያሉ ፈተናዎችን ለመፍታት እየደረጋቸው ያሉ ጥረቶች የሚመሰገኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የምግብ ስርዓትን ለማረጋገጥ ሀገራት ተግባራዊ ምላሽ በመስጠት በቁርጠኝነት መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

እንቅፋቶችን በዘላቂነት ለመፍታት ምክንያት ተኮር ጥረቶች እንዲሁም ውጤታማ ህዝባዊ ንቅናቄን ማድረግ እንደሚገባ ነው ያመላከቱት።

ኢትዮጵያ ይህን አጀንዳ ለመደገፍ ከመቼውም ጊዜ በላይ ቁርጠኛ ሆና እንደምትቀጥልም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026