
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 22/2017 (ኢዜአ)፦የዓለም ሀገራት ለዘላቂ፣ አካታችና የማይበገር የምግብ ሥርዓትን ለመፍጠር የተግባር እርምጃዎችን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ምክትል ዋና ፀሐፊ አሚና መሀመድ ገለጹ።
በኢትዮጵያ፣ ጣሊያንና ተመድ አዘጋጅነት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው ሁለተኛው የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል።
በማጠቃለያ ስነ-ሥርዓቱ ንግግር ያደረጉት የተመድ ምክትል ዋና ፀሐፊ አሚና መሀመድ፥ ጉባኤው ስኬታማ መሆኑን ጠቅሰው፥ ኢትዮጵያ ላደረገችው የተሟላ መስተንግዶ አመስግነዋል።
እ.አ.አ በ2021 ከተካሄደው የመጀመሪያው የምግብ ሥርዓት ጉባኤ በኋላ የኮቪድ 19፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ እና ሌሎች ፈታኝ ሁኔታዎች ቢኖሩም ከ130 በላይ ሀገራት የተቀናጀ ብሔራዊ የምግብ ሥርዓት ሽግግር ፖሊሲ ቀርጸዋል፤ ወደ ተግባርም የገቡ እንዳሉ አውስተዋል።
ሆኖም ኢ-ፍትሐዊነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ፣ ግጭት፣ የሰብዓዊ ድጋፍ መቀነስ አሁንም ፈተና መደቀናቸውን ጠቅሰው፥ ሞራላዊ እሴቶቻችን ጥያቄ ውስጥ ወድቀዋል ነው ያሉት።
የዘንድሮው ጉባኤ ምን ሰራን፣ ምንስ ይጠበቅብናል፣ የሚለውን የፈተሽንበት ብቻ ሳይሆን የዓለም የምግብ ሥርዓት ንቅናቄ በእርግጥም መኖሩን ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል።
ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብ ሥርዓት ለመገንባትም ዓለም አቀፋዊ አንድነትንና የፋይናንስ ትብብር ማደስ፣ ፈጠራ እና አካታችነትን ማጠናከር እንደሚገባም ጠቁመዋል።
አርሶ አደሮችን፣ ሴቶችን፣ ወጣቶችን እና ሥራ ፈጣሪዎችን ያሳተፈ የፖሊሲ እርምጃን ማስፋትም ተገቢ ነው ብለዋል።
ዓለም አቀፍ የልማት ባንኮች፣ ሌሎች የፋይናንስ አመንጪዎች እና የግሉ ዘርፍ ለግብርናው ዘርፍ መጠናከር ኢንቨስት በማድረግ ለምግብ ሥርዓት መሻሻል እንዲሰሩም ጠይቀዋል።
በሀገር በቀል እውቀት የተመሰረተ፣ የአካባቢ፣ የኢኮኖሚና ማህበራዊ መስተጋብርን ያገናዘበ የተቀናጀ ተግባርም ወሳኝ ነው ብለዋል።
በአንድነት ስንሰራ ውጤት ማምጣት እንደምንችል ባለፉት አራት ዓመታት ተመልክተናል ያሉት ምክትል ዋና ፀሐፊዋ፥ መንግሥታት ስኬቱን ማስቀጠል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
በመሆኑም በተጠናከረ የግለት መንፈስ ለህዝብ ተጠቃሚነት፣ ለምድራችን ደህንነት፣ ለሰላም እና ለብልፅግና መትጋት ይገባል ነው ያሉት።
የተባበሩት መንግሥታት፥ ሀገራት የምግብ ሥርዓትን ለማሻሻል ለሚያደርጉት ጥረት ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026