የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የዓለም ሀገራት ለዘላቂ፣ አካታችና የማይበገር የምግብ ሥርዓት በአንድነት ሊተጉ ይገባል

Jul 30, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 22/2017 (ኢዜአ)፦የዓለም ሀገራት ለዘላቂ፣ አካታችና የማይበገር የምግብ ሥርዓትን ለመፍጠር የተግባር እርምጃዎችን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ምክትል ዋና ፀሐፊ አሚና መሀመድ ገለጹ።

በኢትዮጵያ፣ ጣሊያንና ተመድ አዘጋጅነት በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው ሁለተኛው የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል።

በማጠቃለያ ስነ-ሥርዓቱ ንግግር ያደረጉት የተመድ ምክትል ዋና ፀሐፊ አሚና መሀመድ፥ ጉባኤው ስኬታማ መሆኑን ጠቅሰው፥ ኢትዮጵያ ላደረገችው የተሟላ መስተንግዶ አመስግነዋል።

እ.አ.አ በ2021 ከተካሄደው የመጀመሪያው የምግብ ሥርዓት ጉባኤ በኋላ የኮቪድ 19፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ እና ሌሎች ፈታኝ ሁኔታዎች ቢኖሩም ከ130 በላይ ሀገራት የተቀናጀ ብሔራዊ የምግብ ሥርዓት ሽግግር ፖሊሲ ቀርጸዋል፤ ወደ ተግባርም የገቡ እንዳሉ አውስተዋል።

ሆኖም ኢ-ፍትሐዊነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ፣ ግጭት፣ የሰብዓዊ ድጋፍ መቀነስ አሁንም ፈተና መደቀናቸውን ጠቅሰው፥ ሞራላዊ እሴቶቻችን ጥያቄ ውስጥ ወድቀዋል ነው ያሉት።

የዘንድሮው ጉባኤ ምን ሰራን፣ ምንስ ይጠበቅብናል፣ የሚለውን የፈተሽንበት ብቻ ሳይሆን የዓለም የምግብ ሥርዓት ንቅናቄ በእርግጥም መኖሩን ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል።

ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብ ሥርዓት ለመገንባትም ዓለም አቀፋዊ አንድነትንና የፋይናንስ ትብብር ማደስ፣ ፈጠራ እና አካታችነትን ማጠናከር እንደሚገባም ጠቁመዋል።

አርሶ አደሮችን፣ ሴቶችን፣ ወጣቶችን እና ሥራ ፈጣሪዎችን ያሳተፈ የፖሊሲ እርምጃን ማስፋትም ተገቢ ነው ብለዋል።

ዓለም አቀፍ የልማት ባንኮች፣ ሌሎች የፋይናንስ አመንጪዎች እና የግሉ ዘርፍ ለግብርናው ዘርፍ መጠናከር ኢንቨስት በማድረግ ለምግብ ሥርዓት መሻሻል እንዲሰሩም ጠይቀዋል።

በሀገር በቀል እውቀት የተመሰረተ፣ የአካባቢ፣ የኢኮኖሚና ማህበራዊ መስተጋብርን ያገናዘበ የተቀናጀ ተግባርም ወሳኝ ነው ብለዋል።

በአንድነት ስንሰራ ውጤት ማምጣት እንደምንችል ባለፉት አራት ዓመታት ተመልክተናል ያሉት ምክትል ዋና ፀሐፊዋ፥ መንግሥታት ስኬቱን ማስቀጠል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

በመሆኑም በተጠናከረ የግለት መንፈስ ለህዝብ ተጠቃሚነት፣ ለምድራችን ደህንነት፣ ለሰላም እና ለብልፅግና መትጋት ይገባል ነው ያሉት።

የተባበሩት መንግሥታት፥ ሀገራት የምግብ ሥርዓትን ለማሻሻል ለሚያደርጉት ጥረት ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026