
ጅማ፤ ሐምሌ 22/2017(ኢዜአ)፡- ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የማምረት ተግባርን በማጠናከር በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ውጤታማ ስራ መሰራቱን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍስሀ ይታገሱ(ዶ/ር) ገለጹ።
ኮርፖሬሽኑ በሀገሪቱ የሚያስተዳድራቸውን የልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች እና የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ተወካዮች ያሳተፈ የስራ አፈጻጸም ግምገማ በጅማ እያካሄደ ነው።

በመድረኩ የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍስሀ ይታገሱ(ዶ/ር) የተጠናቀቀው በጀት ዓመት የኮርፖሬሽኑ አፈጻጸም የእቅዱን 99 በመቶ መሆኑን ገልጸዋል።
በበጀት ዓመቱ ምርቶችን በሀገር ውስጥ እንዲመረቱ ከማድረግ አንጻር 18 ቢሊዮን ብር የሚገመት ምርት በ11 የኢኮኖሚ ዞኖችና በሁለት ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ መመረቱን ገልጸዋል።
6 ቢሊዮን ብር የገበያ ትስስር ለመፍጠር ታቅዶ 14 ቢሊዮን ብር የገበያ ትስስር በመፍጠር አበረታች እንቅስቃሴ መደረጉንም አነሰተዋል።
ከ80ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ እድል የተፈጠረ ሲሆን፤ 206 ባለሀብቶች በተለያዩ የኢኮኖሚ ዞኖችና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ተሳትፈዋል ብለዋል።
ኮርፖሬሽኑ 11 ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችና ሁለት የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በማስተዳደር የኢንዱስትሪ ልማት ስራዎችን እየሰራ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።
በጅማ የሚገኘውን የኢንዱስትሪ ፓርክ ሁለት አቮካዶ ምርት ላይ የሚሰሩ ካምፓኒዎችና አራት ደግሞ በቡና ፕሮሰሲንግ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች ውል ፈጽመው ማሽነሪዎችን በማስገባት ላይ እንደሚገኙም ተናግረዋል።
በተለይም የጅማ ከተማ የኮሪደር ልማቱ ለኢንዱስትሪ ዘርፍ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ጠቅሰው፤ አሁን ላይ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ከፍተኛ የልማት ፍላጎቶች እየታዩ ነው ብለዋል።
የቦሌ ለሚ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ስራ አስኪያጅ አቶ ትንሳኤ ይማም በበኩላቸው፤ 24 ሼዶች ተገንብተው ስራ መጀመራቸውን ገልጸዋል።

ከ29ሺህ ለሚበልጡ ሰዎች የስራ ዕድል መፍጠር ተችሏል ሲሉም አስታውቀዋል።
የአዳማ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ስራ አስኪያጅ አቶ ጉልላት አበበ፤ በልዩ የኢኮኖሚ ዞኑ የተለያዩ የኢንዱስትሪ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አመልከተው፤ 19 ሼዶች ሲኖሩ፤ 13 ባለሀብቶች መሳተፋቸውን አንስተዋል።

በጋርመንትና ቴክስታይል፣ በኤሌክትሮ መካኒካል እና የመሳሰሉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆነን ገልጸው፤ የተለያዩ ምርቶችም ወደ ውጭ እየላኩ መሆኑን ተናግረዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026