
ጅማ፤ ሐምሌ 22/2017(ኢዜአ)፡- ተኪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የማምረት ተግባርን በማጠናከር በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ውጤታማ ስራ መሰራቱን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍስሀ ይታገሱ(ዶ/ር) ገለጹ።
ኮርፖሬሽኑ በሀገሪቱ የሚያስተዳድራቸውን የልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች እና የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ተወካዮች ያሳተፈ የስራ አፈጻጸም ግምገማ በጅማ እያካሄደ ነው።

በመድረኩ የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍስሀ ይታገሱ(ዶ/ር) የተጠናቀቀው በጀት ዓመት የኮርፖሬሽኑ አፈጻጸም የእቅዱን 99 በመቶ መሆኑን ገልጸዋል።
በበጀት ዓመቱ ምርቶችን በሀገር ውስጥ እንዲመረቱ ከማድረግ አንጻር 18 ቢሊዮን ብር የሚገመት ምርት በ11 የኢኮኖሚ ዞኖችና በሁለት ኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ መመረቱን ገልጸዋል።
6 ቢሊዮን ብር የገበያ ትስስር ለመፍጠር ታቅዶ 14 ቢሊዮን ብር የገበያ ትስስር በመፍጠር አበረታች እንቅስቃሴ መደረጉንም አነሰተዋል።
ከ80ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የስራ እድል የተፈጠረ ሲሆን፤ 206 ባለሀብቶች በተለያዩ የኢኮኖሚ ዞኖችና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ተሳትፈዋል ብለዋል።
ኮርፖሬሽኑ 11 ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችና ሁለት የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በማስተዳደር የኢንዱስትሪ ልማት ስራዎችን እየሰራ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።
በጅማ የሚገኘውን የኢንዱስትሪ ፓርክ ሁለት አቮካዶ ምርት ላይ የሚሰሩ ካምፓኒዎችና አራት ደግሞ በቡና ፕሮሰሲንግ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች ውል ፈጽመው ማሽነሪዎችን በማስገባት ላይ እንደሚገኙም ተናግረዋል።
በተለይም የጅማ ከተማ የኮሪደር ልማቱ ለኢንዱስትሪ ዘርፍ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ጠቅሰው፤ አሁን ላይ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ከፍተኛ የልማት ፍላጎቶች እየታዩ ነው ብለዋል።
የቦሌ ለሚ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ስራ አስኪያጅ አቶ ትንሳኤ ይማም በበኩላቸው፤ 24 ሼዶች ተገንብተው ስራ መጀመራቸውን ገልጸዋል።

ከ29ሺህ ለሚበልጡ ሰዎች የስራ ዕድል መፍጠር ተችሏል ሲሉም አስታውቀዋል።
የአዳማ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ስራ አስኪያጅ አቶ ጉልላት አበበ፤ በልዩ የኢኮኖሚ ዞኑ የተለያዩ የኢንዱስትሪ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አመልከተው፤ 19 ሼዶች ሲኖሩ፤ 13 ባለሀብቶች መሳተፋቸውን አንስተዋል።

በጋርመንትና ቴክስታይል፣ በኤሌክትሮ መካኒካል እና የመሳሰሉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆነን ገልጸው፤ የተለያዩ ምርቶችም ወደ ውጭ እየላኩ መሆኑን ተናግረዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026