የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የክልሉ ምክር ቤት በበጀት ዓመቱ ለሚከናወኑ ስራዎች ማስፈፀሚያ ከ225 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ፀደቀ

Jul 31, 2025

IDOPRESS

ባሕርዳር፤ ሐምሌ 22/2017(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል ምክር ቤት 10ኛ መደበኛ ጉባኤ በ2018 በጀት ዓመት ለሚከናወኑ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ማስፈፀሚያ ከ225 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አፀደቀ።

የክልሉ ገንዘብ ቢሮ ሃላፊ ጥላሁን መሀሪ(ዶ/ር) ረቂቅ በጀቱን ለምክር ቤቱ ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ በጀቱ የክልሉን የመልማት ፍላጎት መሰረት ያደረገ ነው።

በጀቱ የ2018 በጀት ዓመትና የ5 ዓመት የመካከለኛ ዘመን የልማትና የመልካም አስተዳደር ዕቅድ ሰራዎችን ታሳቢ የተደረገ ነው ብለዋል።

ወቅታዊ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ፣ የሪፎርም ስራዎችንና ሌሎች የትኩረት መስኮችን በጀቱ እንደሚያካተት ጠቅሰው፤ ከ2017 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ49 ነጥብ 6 በመቶ ብልጫ እንዳለው አስረድተዋል።

በጀቱ የሚሸፈነው በክልሉ የተለያየ የገቢ፣ ከፌዴራል መንግስትና ከሌሎች ምንጮች እንደሆነም ጠቅሰዋል።

በጀቱ በትክክል የህዝብን የመልማት ፍላጎት መሰረት በማድረግ በቁጠባ ጥቅም ላይ እንዲውል ተገቢው ክትትል፣ ቁጥጥርና ድጋፍ እንደሚደረግ ተመልክቷል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ፤ በጀቱ በፍትሃዊነት የተደለደለ በመሆኑ የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ አግባብ በቁጠባ ጥቅም ላይ እንዲውል የሚደረግ መሆኑን ገልጸዋል።


በየደረጃው ያለው አመራር ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በመሰብሰብ የህዝብን የልማት ፍላጎት በአቅም ልክ ማከናወን ይገባል ብለዋል።

በዚህ በጀት ዓመት 25ቢሊዮን ብር ከህብረተሰብ ተሳትፎ በገንዘብ ለመሰብሰብ መታቀዱን ጠቅሰው፤ ይህ እንዲሳካ መረባረብ እንደሚገባ አመልክተዋል።

የምክር ቤቱ 10ኛ መደበኛ ጉባዔ የቀረበውን ረቂቅ በጀትና የ2017 በጀት ዓመት 13 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት መርምሮ አፅድቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026