የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የተባበሩት ዐረብ ኢምሬቶች ባለሀብቶች በኢትዮጵያ እሴት በሚጨምሩ የኢንቨስትመንት መስኮች ላይ መሰማራት የሚችሉበት ዕድል ተፈጥሯል

Jul 31, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 22/2017(ኢዜአ)፦ የተባበሩት ዐረብ ኢምሬቶች ባለሀብቶች በኢትዮጵያ እሴት በሚጨምሩ የኢንቨስትመንት መስኮች ላይ መሰማራት የሚችሉበት ዕድል መፈጠሩን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ከተባበሩት ዐረብ ኢምሬቶች የአካባቢና የአየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትር አምና አልደሃክ(ዶ/ር) ጋር የሁለቱን ሀገሮች የግብርና ልማት ማጠናከር በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡


ሚኒስትር ግርማ(ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለጹት፤ ውይይቱ በሁለቱ ሀገሮች መካከል ያለውን ስትራቴጂያዊ ግንኙነት ማጠናከር የሚያስችል ነው።

ኢትዮጵያ የቡና፣ የእንስሳት ውጤቶችና ሌሎች የግብርና ምርቶችን ወደ የተባበሩት ዐረብ ኢምሬቶች እንደምትልክ ገልጸው፤ ግንኙነቱን ማስፋት በሚቻልበት ሁኔታ ፍሬያማ ውይይት መደረጉን አብራርተዋል።

ከዚህም ባለፈ የንግድና ኢንቨስትመንት ትስስር ለማጎልበት የሁለቱ ሀገሮች ባለሀብቶች በመደበኛነት በሚገናኙባቸው መንገዶች ላይ መነጋገራቸውን ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ የቴምር ምርትን ለማስፋት ከከሊፋ ፋውንዴሽን ጋር ውይይት መጀመሯን ገልጸው፤ ኢትዮጵያ በመጭው ነሐሴ ወር ለመጀመሪያ ጊዜ የቴምር ጉባኤ እንደምታካሂድ ተናግረዋል።

የተባበሩት ዐረብ ኢምሬቶች ባለሀብቶች በግብርናው ዘርፍ እሴት በሚጨምሩ የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታዎች መመቻቸታቸውን ገልጸዋል፡፡

ሁለተኛው የተመድ የምግብ ስርዓት ጉባኤ ትኩረት የሰጠው ፋይናንስን ወደ ምግብ ሥርዓት እሴት ሰንሰለት ማምጣት ያለመ መሆኑንም አንስተዋል፡፡

የተባበሩት ዐረብ ኢምሬቶች የአካባቢና የአየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትር አምና አልደሃክ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በሁለተኛው የተመድ የምግብ ሥርዓት ስብሰባ መሳተፋቸው ትልቅ ነገር መሆኑን አንስተዋል፡፡


ከስብሰባው ጎን ለጎን በሁለቱ ሀገሮች መካከል ያለውን ስትራቴጂያዊ ግንኙነት በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውንም ገልጸዋል፡፡

ሁለቱ ሀገሮች በግብርናው ዘርፍ ያላቸውን ግንኙነት ለማጠናከር ሊኖር በሚገባው ትብብር ላይ ተወያይተናል ብለዋል።

ሁለቱ ሀገሮች በጽኑ መሰረት ላይ የተገነባ ስትራቴጂያዊ ግንኙነት እንዳላቸው ገልጸው፤ ውይይቱ ከሁለቱ ሀገሮች አልፎ ለቀጣናውና ለዓለም ብልጽግና ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026