የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ብሔራዊ የግብርና ፋይናንስ ትግበራ ፍኖተ ካርታ ይፋ ሆነ

Jul 31, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 23/2017(ኢዜአ)፦የግብርና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ብሔራዊ የግብርና ፋይናንስ ትግበራ ፍኖተ ካርታ ይፋ አደረጉ።

ፍኖተ ካርታው ከ2025 እስከ 2030 ለአምስት ዓመታት ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑ ተጠቁሟል።

ብሔራዊ የግብርና ፋይናንስ ትግበራ ፍኖተ ካርታው በግብርናው ዘርፍ የፋይናንስ ተሳትፎን በማሻሻል ሀገራዊ ግቦችን ለማሳካት ብሎም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ያስችላል ተብሏል።

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ ፍኖተ ካርታው ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ነው ብለዋል።


የግብርናው ዘርፍ ለሀገር የኢኮኖሚ መሠረት መሆኑን ያነሱት ሚኒስትሩ፥የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን ምርታማነትን ለማሳደግ በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ተግባራዊ ባደረገቻቸው የተለያዩ ኢኒሼቲቮች ውጤታማ ስራዎች መሥራቷን ገልጸው፤ የስንዴ ልማት፣ የሌማት ትሩፋት፣የአረንጓዴ አሻራ እንዲሁም በሌሎችም አመርቂ ስራዎች መሠራታቸውን ገልፀዋል።

ዛሬ ይፋ የተደረገው የግብርና ፋይናንስ ፍኖተ ካርታ ለግብርናው ዘርፍ ታሪካዊ ለውጥ የሚያመጣ መሆኑን ጠቁመው፤ የግብርናውን ዘርፍ የፋይናንስ አቅርቦት ለማሻሻል የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል።

የፋይናንስ ተቋማትም ከፋይናንስ አቅራቢነት ባሻገር በሁሉን አቀፍ ዕድገት ላይ የራሳቸውን አሻራ የሚያስቀምጡበት መሆኑንም ተናግረዋል።

ፍኖተ ካርታው ውጤታማ ትግበራ እንዲኖረውም የግብርና ሚኒስቴር ቁርጠኛ መሆኑንም ጠቁመዋል።


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ በበኩላቸው፤ ፍኖተ ካርታው የፋይናንስ ተቋማት የግብርናውን ዘርፍ ውጤታማነት ለማረጋገጥ የሚሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

ፍኖተ ካርታው ለአርሶ አደሮች የተሳለጠ የፋይናንስ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።

በግብርናው ዘርፍ ያሉ ተዋናዮች ሁሉን አቀፍ፣የበለፀገ እና ዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት ምቹ የሆነ የፋይናንስ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማስቻል እንደሚሰራም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026