የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኢትዮጵያ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ትግበራ ሀገራዊ ምርታማነትን ለማሳደግ ገንቢ ሚና ይጫወታሉ

Oct 13, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ጥቅምት 2/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ትግበራ ሀገራዊ የምርታማነት አቅምን ለማሳደግ ገንቢ ሚና እንደሚጫወቱ የተለያየ ዘርፍ አምራች ኢንዱስትሪዎች ገለጹ።

የስንዴ አምራችና ላኪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት ሚሊዮን ቦጋለ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ እየተካሔዱ ያሉ ግዙፍ የልማት ስራዎች ለአምራች ኢንዱስትሪው ተጨማሪ አቅም የፈጠሩ ናቸው።

በተለይም ባለፉት የለውጥ ዓመታት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ጨምሮ የኢንዱስትሪ ዘርፉን ምርታማነት መጨመር የሚያስችል የአሰራር ስርዓት መዘርጋቱ ጉልህ አስተዋጽኦ አበርክቷል።

በተጨማሪም በመሰረተ ልማት፣በኃይል አቅርቦት፣በግብዓትና በቴክኖሎጂ ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራትም እንዲሁ ለኢንዱስትሪ ዘርፉ ማንሰራራት አይነተኛ ሚና አላቸው ብለዋል።

በተለይም በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የመሰረት ድንጋይ የተቀመጠለት የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ለግብርና ምርታማነት ትልቅ እድል ይዞ የሚመጣ ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ በግብርና ዘርፍ እየተገኘ ያለውን ስኬት በእጥፉ ለማሳደግና በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን ጥረት ከዳር ለማድረስ አይነተኛ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል።

በተጨማሪም የአፈር ማዳበሪያን ከውጭ ለማስገባት ይወጣ የነበረውን የውጭ ምንዛሪ በአገር ውስጥ መተካት የሚያስችል መሆኑ ለኢኮኖሚው እድገት ወሳኝ እንደሆነ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መሰረታዊ ብረታብረትና ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪዎች ማህበር ስራ አስኪያጅ ሰለሞን ሙሉጌታ በበኩላቸው፤ እንደ ሀገር ተግባራዊ የተደረጉ ፕሮጀክቶች ለአምራች ዘርፉ ምርታማነት ትልቅ እድል ይዘው የመጡ ናቸው።

ለፕሮጀክቶቹ ግንባታ የሚሆን በቂ የብረታብረት ግብዓትን ለማቅረብ ተጨማሪ የማምረት አቅምን የሚፈጥር ነው ብለዋል።

መንግስት በኢንዱስትሪ ዘርፍ በስፋት የሚፈለገውን የሃይል አቅርቦት ለማሟላትና አማራጭ የሃይል አቅርቦትን ለመጨመር የሚያደርገው ጥረት በእጅጉ የሚበረታታ መሆኑን አንስተዋል።

በተለይም በቅርቡ የተመረቁት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እና የኦጋዴን ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ የመጀመሪያ ዙር ፕሮጀክቶች ለብረታብረት ኢንዱስትሪዎች ተጨማሪ የሃይል አቅርቦትን የሚሰጡና ትልቅ ጠቀሜታ ያላቸው መሆናቸውን አንስተዋል።

ይህም ለአገር ኢኮኖሚያዊ እድገት ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ነው ብለዋል።

የማሽነሪ አምራቾች ማህበር ሊቀመንበር አክሊሉ አባተ እንዲሁ በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረጉ ያሉ የልማት ስራዎች የአመራር ብቃትና ቁርጠኝነትን በተግባር ያሳዩ ናቸው ብለዋል።

ቀደም ሲል እንደ ሀገር በሃይል እጥረት ምክንያት ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅማቸው ዝቅተኛ እንደነበር አስታውሰው፤ በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ መሻሻሎች እንዳሉ አንስተዋል።

ይህም የአምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም እንዲጨምር እድል የፈጠረና ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ እንዲያጎላ አስቸሏል ነው ያሉት።

በአሁኑ ወቅት ተግባራዊ የተደረጉ ግዙፍ ፐሮጀክቶችን ጨምሮ መሰረት የተቀመጠላቸው ፕሮጀክቶች የኢንዱስትሪዎችን ጫና በማቃለል ረገድ አይነተኛ ሚና አላቸው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026