የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኦሮሚያ ክልል የሕዝቡን የመልካም አስተዳደርና የመልማት ጥያቄዎች በተሻለ መልኩ መመለስ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው

Oct 14, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፡- በኦሮሚያ ክልል የሕዝቡን የመልካም አስተዳደርና የመልማት ጥያቄዎች በተሻለ መልኩ መመለስ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ ተናገሩ።

በክልሉ የ2018 የስራ ዘመን የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የመንግስትና የፓርቲ የስራ ዕቅድ ክንውን ግምገማ የክልሉ ፕሬዚዳንትን ጨምሮ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ሰአዳ አብዱራህማን፣ ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ አወሉ አብዲና በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከፍያለው ተፈራ በተገኙበት መካሄድ ጀምሯል።


በግምገማው መደረክ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ፣ የክልሉ አመራር በተገኙ ስኬቶች ሳይዘናጋ ቀጣይ ተልዕኮን በአግባቡ በመፈጸም የሕዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ መዘጋጀት አለበት ብለዋል።

ባለፉት ዓመታት የክልሉ አመራር የመፈጸምና የማስፈፀም አቅም እያደገ በመምጣቱ የሕዝቡን የማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።

በተለይም በክልሉ መንግስት ተቀርጸው እየተተገበሩ ያሉ የልማት ኢኒሼቲቮች በታቀደው መልኩ ውጤታማ እንዲሆኑ ርብርቡ ሊጠናከር እንደሚገባ አመልክተዋል።

ከልማት ስራዎች ጎን ለጎን ከቀበሌ ጀምሮ የአገልግሎት አሰጣጥ ፍትሃዊና ቀልጣፋ እንዲሆን የተጀመሩ ስራዎች እንዲሰፉም ይደረጋል ብለዋል።

ዛሬ በተጀመረው መድረክም የሕዝቡን የመልካም አሰተዳደር፣ ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ጥያቄዎች በተሻለ መልክ መመለስ በሚያስችሉ ተግባራት ላይ ምክክር ይደረጋል ብለዋል።

የሕዝብና የመንግስትን አቅም አቀናጅቶ ለማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ከማዋል አንፃር የተሰሩ ስራዎችና ቀጣይ አቅጣጫ የመድረኩ ትኩረት መሆኑን ገልጸዋል።


በብልፅግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከፍያለው ተፈራ በበኩላቸው፤ የመጀመሪያው ሩብ ዓመት አፈፃፀም ከዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ ተጨባጭ ውጤቶች የተገኙበት ነው ብለዋል።

የክልሉን ሰላም ከማፅናት አኳያ የፀጥታ መዋቅሩን በየደረጃው የማጠናከር ስራ መከናወኑን ጠቅሰው ፤ በዚሕም ሰላም ማስፈን መቻሉን ተናግረዋል።

ከአገልግሎት አሰጣጥ አንጻርም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአምስት የክልሉ ከተሞች በማስጀመር የአገልግሎት አሰጣጥን በቴክኖሎጂ የተደገፈ ፍትሃዊና ቀልጣፋ ለማድረግ ተሞክሯል ነው ያሉት።

ዛሬ በተጀመረው መድረክም የነበሩ ክፍተቶችን በግምገማና በአግባቡ በመለየት ቀጣይ አቅጣጫ የምናስቀምጥበት ይሆናል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026