🔇Unmute
ድሬዳዋ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፡- ስማርት ድሬዳዋን ዕውን ለማድረግ እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በጥራትና በስፋት ለማዳረስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ገለጹ።
በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለሚገነባው የአይ ሲ ቲ ትምህርትና ስልጠና ልህቀት ማዕከል ዛሬ የመሠረት ድንጋይ ተቀምጧል።

የመሠረት ድንጋዩን ያስቀመጡት ከንቲባ ከድር ጁሃር፣ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአስተዳደሩ ምክርቤት የመንግስት ተጠሪ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ እና የካቢኔ አባላት ናቸው።
በዚህ ወቅት ከንቲባው እንደገለጹት፤ ማዕከሉ ስማርት ድሬዳዋን ዕውን ለማድረግ ለሚከናወነው ሥራ ወሳኝ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
የልህቀት ማዕከሉ በተጨማሪም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በጥራትና በስፋት ለማዳረስ በሚደረገው ጥረት መሠረታዊ ሚና እንደሚኖረው ነው ያመለከቱት።
ባለ አምስት ወለል የሚሆነው የልቀት ማዕከል ግንባታ ሥራ በተያዘለት የ14 ወራት ጊዜ ውስጥ በጥራትና በፍጥነት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር ይደረጋል ብለዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአስተዳደሩ ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ኢብራሂም ዩሱፍ በበኩላቸው ለድሬዳዋ ዲጂታል የለውጥ ጉዞ ዕውን መሆንና በዘርፉ ሥራ ፈጣሪ ትውልድ ለመገንባት ማዕከሉ የጎላ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል።
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሰላሃዲን አብዱልሃሚድ በበኩላቸው፤ ማዕከሉ በውስጡ 42 ክፍሎች እንደሚኖሩት ገልጸዋል።
የኮምፒውተር ላቦራቶሪ፣ የምርምርና የመማሪያ ክፍሎች፣ እንዲሁም የዲዛይን ስቱዲዮ፣ የኮንፍረንስ እና የዲጂታል ቤተ-መጻህፍትን እንደሚያካትም ተመላክቷል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026