🔇Unmute
ድሬዳዋ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፡- ስማርት ድሬዳዋን ዕውን ለማድረግ እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በጥራትና በስፋት ለማዳረስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ገለጹ።
በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለሚገነባው የአይ ሲ ቲ ትምህርትና ስልጠና ልህቀት ማዕከል ዛሬ የመሠረት ድንጋይ ተቀምጧል።

የመሠረት ድንጋዩን ያስቀመጡት ከንቲባ ከድር ጁሃር፣ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአስተዳደሩ ምክርቤት የመንግስት ተጠሪ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ እና የካቢኔ አባላት ናቸው።
በዚህ ወቅት ከንቲባው እንደገለጹት፤ ማዕከሉ ስማርት ድሬዳዋን ዕውን ለማድረግ ለሚከናወነው ሥራ ወሳኝ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
የልህቀት ማዕከሉ በተጨማሪም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በጥራትና በስፋት ለማዳረስ በሚደረገው ጥረት መሠረታዊ ሚና እንደሚኖረው ነው ያመለከቱት።
ባለ አምስት ወለል የሚሆነው የልቀት ማዕከል ግንባታ ሥራ በተያዘለት የ14 ወራት ጊዜ ውስጥ በጥራትና በፍጥነት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር ይደረጋል ብለዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአስተዳደሩ ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ኢብራሂም ዩሱፍ በበኩላቸው ለድሬዳዋ ዲጂታል የለውጥ ጉዞ ዕውን መሆንና በዘርፉ ሥራ ፈጣሪ ትውልድ ለመገንባት ማዕከሉ የጎላ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል።
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሰላሃዲን አብዱልሃሚድ በበኩላቸው፤ ማዕከሉ በውስጡ 42 ክፍሎች እንደሚኖሩት ገልጸዋል።
የኮምፒውተር ላቦራቶሪ፣ የምርምርና የመማሪያ ክፍሎች፣ እንዲሁም የዲዛይን ስቱዲዮ፣ የኮንፍረንስ እና የዲጂታል ቤተ-መጻህፍትን እንደሚያካትም ተመላክቷል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026