🔇Unmute
ድሬዳዋ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፡- ስማርት ድሬዳዋን ዕውን ለማድረግ እና መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በጥራትና በስፋት ለማዳረስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ገለጹ።
በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለሚገነባው የአይ ሲ ቲ ትምህርትና ስልጠና ልህቀት ማዕከል ዛሬ የመሠረት ድንጋይ ተቀምጧል።

የመሠረት ድንጋዩን ያስቀመጡት ከንቲባ ከድር ጁሃር፣ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአስተዳደሩ ምክርቤት የመንግስት ተጠሪ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ እና የካቢኔ አባላት ናቸው።
በዚህ ወቅት ከንቲባው እንደገለጹት፤ ማዕከሉ ስማርት ድሬዳዋን ዕውን ለማድረግ ለሚከናወነው ሥራ ወሳኝ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
የልህቀት ማዕከሉ በተጨማሪም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በጥራትና በስፋት ለማዳረስ በሚደረገው ጥረት መሠረታዊ ሚና እንደሚኖረው ነው ያመለከቱት።
ባለ አምስት ወለል የሚሆነው የልቀት ማዕከል ግንባታ ሥራ በተያዘለት የ14 ወራት ጊዜ ውስጥ በጥራትና በፍጥነት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር ይደረጋል ብለዋል።
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአስተዳደሩ ምክር ቤት የመንግስት ተጠሪ ኢብራሂም ዩሱፍ በበኩላቸው ለድሬዳዋ ዲጂታል የለውጥ ጉዞ ዕውን መሆንና በዘርፉ ሥራ ፈጣሪ ትውልድ ለመገንባት ማዕከሉ የጎላ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል።
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሰላሃዲን አብዱልሃሚድ በበኩላቸው፤ ማዕከሉ በውስጡ 42 ክፍሎች እንደሚኖሩት ገልጸዋል።
የኮምፒውተር ላቦራቶሪ፣ የምርምርና የመማሪያ ክፍሎች፣ እንዲሁም የዲዛይን ስቱዲዮ፣ የኮንፍረንስ እና የዲጂታል ቤተ-መጻህፍትን እንደሚያካትም ተመላክቷል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025