የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በምሥራቅ ወለጋ ዞን  በበጋ መስኖ የስንዴ ልማት ተጠናክሮ ቀጥሏል

Oct 17, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ነቀምቴ ፤ ጥቅምት 6/2018 (ኢዜአ) ፡- በምሥራቅ ወለጋ ዞን በበጋ መስኖ የሚካሄድ የስንዴ ልማት ተጠናክሮ መቀጠሉን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ።

በዞኑ ጉቶ ጊዳ ወረዳ ጋሪ ቀበሌ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የማስጀመሪያ መርሀ ግብር ተካሂዷል።

በዚህ ወቅት የምሥራቅ ወለጋ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ሀላፊ ዶክተር ደረጄ ብርሃኑ እንደተናገሩት፤ በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ሂደት ውስጥ የግብርናው ዘርፍ ጉልህ ድርሻ አለው።


በዞኑ ባለፉት ዓመታት በበጋ መስኖ የስንዴ ልማት ላይ የተገኘውን ውጤት መሰረት በማድረግ በቀጣይ በተሻለ መልኩ አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በዘንድሮ የበጋ ወቅትም የስንዴ ልማቱን አጠናክሮ ለማስቀጠል አርሶ አደሮችን በመደገፍ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረው፤ ለአርሶ አደሮቹ የግብዓት አቅርቦት ማመቻትን ጨምሮ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል።

የጉቶ ጊዳ ወረዳ የግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ሀላፊ አቶ ገረመው አስፋው በበኩላቸው፤ በወረዳው በኩታ ገጠም በመስኖ ስንዴን ለማምረት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።


በወረዳው በጋሪ ቀበሌ መልካ ዶሪ ክላስተር ጨምሮ 15 ሄክታር መሬት ላይ ልማቱ እየተካሄደ ነው ብለዋል።

ከአካባቢው አርሶ አደሮች መካከል ታሪኩ ስጦታው በሰጡት አስተያየት፤ አምና በግማሽ ሄክታር መሬት ስንዴን በመስኖ በማልማት አስር ኩንታል ምርት ማግኘታቸውን በማስታወስ ዘንድሮም ተግባሩን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026