የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ታማኝ ግብር ከፋዮች ለመዲናዋ ዕድገት፣ ልማትና ለትውልድ ግንባታ ደማቅ አሻራ በማኖር ላይ ናቸው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Oct 17, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፦ ታማኝ ግብር ከፋዮች ለመዲናዋ ዕድገት፣ ልማትና በትውልድ ግንባታ ስራ ላይ ደማቅ አሻራ በማኖር ላይ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለታማኝ ግብር ከፋዮች እውቅና መርሐ ግብር እያካሄደ ይገኛል፡፡

በመርሐ ግብሩ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አፈ-ጉባኤ ቡዜና አልከድር፣ የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት፤ ግብር ከፋዮች ለታማኝነታቸውና ለከተማቸው ልማት ላደረጉት አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በከተማዋ የሚሰበሰበው ገቢ ከፍተኛ ዕድገት እያሳየ መሆኑን ጠቁመው በ2010 በጀት ዓመት 33 ቢሊዮን ብር እንደነበር አስታውሰው በ2017 በጀት ዓመት ወደ 233 ቢሊዮን ብር ማደጉን ገልጸዋል፡፡


የገቢ ዕድገቱ የኢኮኖሚን መነቃቃትና ለውጥ በግልጽ የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመው በከተማዋ ጤናማ የገቢ አሰባሰብና የታክስ አስተዳደር ስርዓት በተሻለ መልኩ በመተግበር የተሰበሰበው ግብር ለከተማዋ ዕድገትና መዘመን እየዋለ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የተሰበሰበውን ግብር በታማኝነት ስራ ላይ በማዋል እያስመዘገብናቸው የምንገኛቸው ተጨባጭ ለውጦችና ልማቶች ግብር ከፋዩ የበለጠ ሃብት እንዲፈጥር የሚያስችሉ ናቸው ብለዋል፡፡

የህዝቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጡ የሚገኙ እና አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብ ያደረጉ የኮሪደርና የወንዝ ልማት ዳርቻ ልማቶችን ጨምሮ የተሰሩ የልማት ስራዎች በሚሰበሰበው ገቢ መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡

በዚህም በርካታ የሥራ ዕድሎች መፈጠራቸውን ጠቁመው ኢኮኖሚው እየተነቃቃ፣ ከተማዋ በእጅጉ እየተለወጠችና ተቋማት እየዘመኑ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

የአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ መዳረሻ መሆን መጨመሩን አንስተው ከላይ የተገለጹት ለግብር ከፋዩ ስራ መስፋፋትና መላቅ ትልቅ አስተዋጽኦ የሚያበርክቱ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡


ግብር የፍትሐዊነት ማስፈኛ መሳሪያ መሆኑን ጠቁመው በየዓመቱ ከ14 ቢሊዮን ብር በላይ ድጎማ በማድረግ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች መደገፍ ማስቻሉን ጠቅሰው፥ በትምህርት ቤት ምገባም ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ ተማሪዎች በቀን ሁለት ጊዜ እንዲመገቡ እያገዘን ነው ብለዋል፡፡

የግብር ከፋዮች ለከተማ እደገት ቀንዲል ናቸው ያሉት ከንቲባዋ ታማኝ ግብር ከፋዮች ለከተማዋ ዕድገት ግዴታቸውን በመወጣት ላይ መሆናቸውንም አክለዋል።

በዚህም በከተማዋ ዕድገትና ለውጥ እንዲሁም ለትውልድ እየተሰራ ባለው አጠቃላይ ስራ ዘመን ተሻጋሪ ደማቅ አሻራቸውን እያሳረፉ መሆኑን በአፅንኦት ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026