የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

አስተዳደሩ የሚቃጡ የሳይበር ጥቃቶችን ከመመከት አንጻር እያሳየ ያለውን ውጤታማ ሥራዎች ማጠናከር ይገባዋል - ቋሚ ኮሚቴው

Oct 29, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 17/2018(ኢዜአ)፦ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በሀገር ላይ የሚቃጡ የሳይበር ጥቃቶችን ከመመከት አንጻር እያሳየ ያለውን ውጤታማ ሥራዎች አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጸ።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደርን የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን ገምግሟል።


የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ ባቀረቡት ሪፖርት፤ ሀገራዊ የሳይበር ቁጥጥርን ከማጎልበት አኳያ ውጤታማ ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በዚህም የዲጂታል ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ቁልፍ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ተልዕኮ ተኮር ምርትና አገልግሎት ተደራሽነትን ከማስፋት አኳያም ውጤታማ ሥራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ ቁልፍ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ላይ የሚቃጡ የሳይበር ጥቃቶችን ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም መገንባቱን ጠቁመው፤ በሩብ ዓመቱ ለተመዘገቡ 13 ሺህ 443 የጥቃት ሙከራዎች ምላሽ መስጠት መቻሉን ተናግረዋል።

በሩብ ዓመቱ በርካታ አገልግሎቶች ተደራሽ መደረግ መቻላቸውን ጠቁመው፤ የኤሌክትሮኒክስ ደረሰኝ አስተዳደር ስርዓት ተጠናቆ በይፋ መመረቁንም ገልጸዋል።

በተጨማሪም በሩብ ዓመቱ የኤሮ-አባይ የድሮን ማምረቻ፣ የኮንስትራክሽን ሬጉላቶሪ ስርዓት፣ ለበርካታ ከተሞች የካደስተር ኢ-ላንድ መተግበሪያን ጨምሮ ሌሎችንም ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ጠቁመዋል።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላትም የተቋሙን የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈጻጸም በማድነቅ ምላሽና ማብራሪያ የሚፈልጉ ጉዳዮችንም አቅርበዋል።

ከእነኚህም መካከል የሀገርን የሳይበር ሉዓላዊነት ለማስጠበቅና የሳይበር ጥቃትን ቀድሞ ከመከላከል አንጻር የተቋሙ አሁናዊ ቁመና ምን እንደሚመስል ጠይቀዋል።

በተጨማሪም የተቋሙ ሀገራዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ አጋርነት፣ ትብብርና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከውጤት አንጻር ምን ማሳያ አለው የሚሉ ጥያቄዎችን አንስተዋል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና ማብራሪያዎች ምላሽ የሰጡ ሲሆን፣ የሳይበር ደህንነትን ከማስጠበቅ አኳያ አስተማማኝ ሁኔታ ላይ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል ጉታ የምላሽ አሰጣጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን ጠቁመው፤የተቋሙ ዝግጁነትም እያደገ መሆኑን አንስተዋል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አማካሪ ፍቅረስላሴ ጌታቸው ተቋሙ የተለያዩ ስምምነቶችን ከመፈራረም ባሻገር ስምምነቶችን ወደ ተግባር በመለወጥ ትልቅ ፋይዳ እያስገኘ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የኢንፎርሜሽን አሹራንስ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ተወካይ ሃኒባል ለማ በበኩላቸው፤ የስትራቴጂክ ዕቅዶችን በሶስት ዓመታት ውስጥ ተግባራዊ ማድረግ የሚያስችል ዕቅድ መያዙን ጠቁመው፤ ይህም የመሰረተ ልማት ግንባታንና ሥራን መሠረት ያደረገ ነው ብለዋል።


በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሰቢ ፈቲህ ማሕዲ (ዶ/ር) በሰጡት ማጠቃለያ፣ አስተዳደሩ የሚቃጡ የሳይበር ጥቃቶችን ከመመከት አንጻር እያሳየ ያለውን ውጤታማ ተግባራት አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።

በቅድመ መከላከልና ዝግጁነት የተሰሩ አበረታች ሥራዎችን ማጠናከር እንዳለበት ጠቁመው፤ ተቋሙ ብቁ የሰው ኃይልን ከማፍራት አኳያ የጀመራቸውን ውጤታማ ሥራዎች አጠናክሮ እንዲቀጥልም አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025