🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 23/2018(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ከዓለም ሀገራት ጋር ትገናኝበት የነበረውን የባሕር በር መጠየቋ መሠረታዊ ጥያቄ በመሆኑ ሁላችንም የሚጠበቅብንን መወጣት አለብን ሲሉ በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ዲን እና ተመራማሪ አበበ አኖ (ዶ/ር) ገለጹ።
አበበ አኖ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ኢትዮጵያ የባሕር በር እንድታገኝ የሚደረገው ጥረት መሠረታዊ ጉዳይ መሆኑን በአጽንኦት ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የራሷ የሆነ የባሕር በር ከነበራቸው ቀደምት ሀገራት መካከል እንደነበረች አውስተዋል።
በነበራት የባሕር በርም ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች ጋር በንግድ፣ በጉብኝት እንዲሁም በሌሎች ሥራዎች ጥብቅ ቁርኝት እንደነበራት አስታውሰው፤ ይህንም ታሪክ እንደሚመሠክርም አስረድተዋል።
ነገር ግን ከዚህ ቀደም በነበረው የፖለቲካ ሁኔታ በተፈጸመ ታሪካዊ ስህተት የነበራትን ባሕር በር እንድታጣ መደረጉ አስቆጭም፤ አሳዛኝም መሆኑን ተናግረዋል።
በአንድ ወቅት የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ ፍላጎት ሳይኖር በአንድ የፖለቲካ ቡድን ውሳኔ ብቻ የባሕር በርን ያህል ለዘርፈ-ብዙ ዕድገት ወሳኝ አበርክቶ ያለው ሐብት መነፈግ አንገብጋቢ ነው ብለዋል።
ተጨማሪ ቁጭት የሚፈጥረው ደግሞ ከለውጡ በፊት ለበርካታ ዓመታት የባሕር በር ጥያቄው በመንግሥት ደረጃ ‘ጆሮ ዳባ’ መባሉ ነው ይላሉ።
የሆነው ሆኖ የባሕር በሯ የተወሰደበትም ሆነ ምንም እንዳልተፈጠረ ዝም የተባለበት ሁኔታ ቢያስቆጭም፤ በለውጡ መንግስት ኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት እንዳለባት ታምኖ አሁን ጥረቶች መጀመራቸው ተገቢ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ የነበራትን ተቀምታ፣ ከቀይ ባሕር በቅርብ ርቀት ላይ ሆና፣ የግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት ሆና እና ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ ይዛ የበይ ተመልካች ልትሆን እንደማይገባ አብራርተዋል።
ስለሆነም የራሷን ግዛት አሳማኝ ባልሆነ ምክንያት ያጣች ሀገር መሆኗን የሀገራት መሪዎች እና ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ተገንዝቦ እንዲያግዝ ሁላችንም የሚጠበቅብንን መወጣት ይገባናል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ሕዝብም የባሕር በር ለበለጸገች ሀገር አስፈላጊ መሆኑን ተረድቶ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት መዋጣት እንዳለበትም አመላክተዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025