🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 23/2018(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ከዓለም ሀገራት ጋር ትገናኝበት የነበረውን የባሕር በር መጠየቋ መሠረታዊ ጥያቄ በመሆኑ ሁላችንም የሚጠበቅብንን መወጣት አለብን ሲሉ በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የማኅበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ ዲን እና ተመራማሪ አበበ አኖ (ዶ/ር) ገለጹ።
አበበ አኖ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ኢትዮጵያ የባሕር በር እንድታገኝ የሚደረገው ጥረት መሠረታዊ ጉዳይ መሆኑን በአጽንኦት ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የራሷ የሆነ የባሕር በር ከነበራቸው ቀደምት ሀገራት መካከል እንደነበረች አውስተዋል።
በነበራት የባሕር በርም ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች ጋር በንግድ፣ በጉብኝት እንዲሁም በሌሎች ሥራዎች ጥብቅ ቁርኝት እንደነበራት አስታውሰው፤ ይህንም ታሪክ እንደሚመሠክርም አስረድተዋል።
ነገር ግን ከዚህ ቀደም በነበረው የፖለቲካ ሁኔታ በተፈጸመ ታሪካዊ ስህተት የነበራትን ባሕር በር እንድታጣ መደረጉ አስቆጭም፤ አሳዛኝም መሆኑን ተናግረዋል።
በአንድ ወቅት የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ ፍላጎት ሳይኖር በአንድ የፖለቲካ ቡድን ውሳኔ ብቻ የባሕር በርን ያህል ለዘርፈ-ብዙ ዕድገት ወሳኝ አበርክቶ ያለው ሐብት መነፈግ አንገብጋቢ ነው ብለዋል።
ተጨማሪ ቁጭት የሚፈጥረው ደግሞ ከለውጡ በፊት ለበርካታ ዓመታት የባሕር በር ጥያቄው በመንግሥት ደረጃ ‘ጆሮ ዳባ’ መባሉ ነው ይላሉ።
የሆነው ሆኖ የባሕር በሯ የተወሰደበትም ሆነ ምንም እንዳልተፈጠረ ዝም የተባለበት ሁኔታ ቢያስቆጭም፤ በለውጡ መንግስት ኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት እንዳለባት ታምኖ አሁን ጥረቶች መጀመራቸው ተገቢ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ የነበራትን ተቀምታ፣ ከቀይ ባሕር በቅርብ ርቀት ላይ ሆና፣ የግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት ሆና እና ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ ይዛ የበይ ተመልካች ልትሆን እንደማይገባ አብራርተዋል።
ስለሆነም የራሷን ግዛት አሳማኝ ባልሆነ ምክንያት ያጣች ሀገር መሆኗን የሀገራት መሪዎች እና ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ተገንዝቦ እንዲያግዝ ሁላችንም የሚጠበቅብንን መወጣት ይገባናል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ሕዝብም የባሕር በር ለበለጸገች ሀገር አስፈላጊ መሆኑን ተረድቶ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት መዋጣት እንዳለበትም አመላክተዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026