የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በበጋ መስኖ ለገበያ ጭምር የሚቀርብ ስንዴ በማምረት ተጠቃሚ ሆነናል- አርሶ አደሮች

Nov 6, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር ፤ ጥቅምት 25/2018(ኢዜአ) ፡- በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ለገበያ ጭምር የሚቀርብ በማምረት ተጠቃሚ መሆናቸውን በማዕከላዊ ጎንደር ዞን አርሶ አደሮች ገለጹ።

በዞኑ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የማስጀመሪያ መርሀ ግብር ዛሬ በወገራ ወረዳ ባልደርጌ ቀበሌ ተካሂዷል።

ከቀበሌው ነዋሪዎች ውስጥ አርሶአደር ተሾመ ተስፋዬ በሰጡት አስተያየት፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ከጀመሩ ሶስት ዓመት እንደሆናቸው ተናግረዋል።

በዚህም ሲያገኙት የቆየው ምርት ከፍጆታቸው የተረፈውን ለገበያ በማቅረብ የልጆቻውን የትምህርት ወጪ በመሸፈን ጭምር ተጠቃሚ እንደሆኑ ገልጸዋል።

ይህንን ለማስፋትም በዘንድሮው የበጋ ወቅት ግማሽ ሄክታር መሬታቸውን በበጋ መስኖ የስንዴ ሰብል ለማዋል የእርሻ ስራ መጀመራቸውን አንስተዋል።

ሌላው የቀበሌው አርሶአደር ተስፉ ሙጨ፤ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት እየተሳተፉ እያገኙ ካሉት ትርፍ ምርት ሽያጭ የገቢ አቅማቸው እያደገ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ባለፈው ዓመት በስንዴ ልማቱ ባገኙት ተጨማሪ ገቢ አንድ በሬ መግዛት እንደቻሉ አውስተዋል።

በዘንድሮ በጋም ግማሽ ሄክታር መሬታቸውን በሰንዴ ሰብል በመሸፈን 20 ኩንታል ምርት እንደሚጠብቁ ገልጸዋል። ።

የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የስራ ባሕላችንን በመቀየር የድሕነት መውጫ መንገድ ሆኖናል ያሉት ደግሞ ሌላው አርሶ አደር አስረስ መላኩ ናቸው።

ከመኸር እርሻ በተጨማሪ በጋውን በመስኖ ስንዴ በማልማት ያገኙት ትርፍ ምርት ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚነታችን እንዲጨምር ምቹ ሁኔታ ተፈጥሮልናል ብለዋል።

የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ ንጉሴ ማለደ በበኩላቸው ፤ በዘንድሮው የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት 20ሺህ ሄክታር መሬት በማልማት ከ780 ሺህ ኩንታል በላይ ለማምረት ታቅዶ እየተሰራ ነው ብለዋል።

ምርታማነቱን ለማሳደግም ከ50 ሺህ ኩንታል በላይ ማዳበሪያና ምርጥ የስንዴ ዘር የማቅረብ ስራ መጀመሩን ጠቅሰው፤ ከ6ሺህ በላይ ነባርና አዲስ የውሃ መሳቢያ ሞተሮች ጥቅም ላይ እንደሚውሉ አስረድተዋል።

የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማሳደግ የሚያግዙ ሌሎች የተሻሻሉ የግብርና አሰራሮች በስፋት ለመተግበር እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።

በበጋ መስኖ ስንዴ ልማቱ ማስጀመሪያ መረሃ ግብር ላይ አርሶ አደሮችን ጨምሮ የዞኑና የወረዳው አመራሮችና የግብርና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026