🔇Unmute
ሰቆጣ ፤ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፦በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ከ4 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ የማልማት ስራ መጀመሩን የብሄረሰብ አስተዳደሩ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
መምሪያው የ2018 የመስኖ ልማት የንቅናቄ መድረክ ዛሬ አካሂዷል።
የመምሪያው ሃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት በብሄረሰብ አስተዳደሩ የሚስተዋለውን የምግብ ዋስትና ችግር ለመቅረፍ የመስኖ ልማት ዋና አቅም ነው።
በዚህም በያዝነው የበጋ ወቅት 4 ሺህ 738 ሄክታር መሬት በሁለት ዙር መስኖ በማልማት ከ900 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ገልጸዋል።
በመስኖ ከሚለማው መሬት ውስጥም አንድ ሺህ ሄክታር የሚሆነው መሬት በበጋ ስንዴ የሚሸፈን ሲሆን ቀሪው ደግሞ በሌሎች ሰብሎችና የአትክልት ምርቶች እንደሚለማ ተናግረዋል።
እስካሁን በተደረገው ጥረት ከአንድ ሺህ ሄክታር በላይ መሬት መልማቱን ጠቁመው ምርታማነቱን ለማሳደግ የማዳበሪያና ምርጥ ዘር እየቀረበ መሆኑን አስታውቀዋል።
በብሄረሰብ አስተዳደሩ በባለፈው ዓመት በመስኖ ከለማው መሬት ላይ 810 ሺህ 637 ኩንታል ምርት መሰብሰብ መቻሉን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026