የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በብሄረሰብ አስተዳደሩ ከ4 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ የማልማት ስራ ተጀምሯል

Nov 6, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰቆጣ ፤ጥቅምት 26/2018(ኢዜአ)፦በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ከ4 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት በመስኖ የማልማት ስራ መጀመሩን የብሄረሰብ አስተዳደሩ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

መምሪያው የ2018 የመስኖ ልማት የንቅናቄ መድረክ ዛሬ አካሂዷል።

የመምሪያው ሃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት በብሄረሰብ አስተዳደሩ የሚስተዋለውን የምግብ ዋስትና ችግር ለመቅረፍ የመስኖ ልማት ዋና አቅም ነው።

በዚህም በያዝነው የበጋ ወቅት 4 ሺህ 738 ሄክታር መሬት በሁለት ዙር መስኖ በማልማት ከ900 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ገልጸዋል።

በመስኖ ከሚለማው መሬት ውስጥም አንድ ሺህ ሄክታር የሚሆነው መሬት በበጋ ስንዴ የሚሸፈን ሲሆን ቀሪው ደግሞ በሌሎች ሰብሎችና የአትክልት ምርቶች እንደሚለማ ተናግረዋል።

እስካሁን በተደረገው ጥረት ከአንድ ሺህ ሄክታር በላይ መሬት መልማቱን ጠቁመው ምርታማነቱን ለማሳደግ የማዳበሪያና ምርጥ ዘር እየቀረበ መሆኑን አስታውቀዋል።

በብሄረሰብ አስተዳደሩ በባለፈው ዓመት በመስኖ ከለማው መሬት ላይ 810 ሺህ 637 ኩንታል ምርት መሰብሰብ መቻሉን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026