🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 30/2018(ኢዜአ)፦ ኤሌክትሪክ እንዳይቋረጥና ሲቋረጥም ፈጣን መረጃ በመስጠት የሃይል ተደራሽነትን ማስፋት የሚያስችል "ስካዳ" የተሰኘ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ገለጸ፡፡
የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አንዋር አብራር ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት የዜጎችን የኑሮ ደረጃ በማሻሻልና የኢንዱስትሪ ልማትን በማስፋፋት ለኢኮኖሚያዊ ዕድገት ወሳኝ ነው፡፡
የለውጡ መንግስት አዳዲስ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማትን በማስፋፋት፣ ብዝኃ የሀይል ማመንጫዎችን በማስፋትና አዳዲስ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ፍትሐዊ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡
ያረጁ የኤሌክትሪክ መስመሮችን መልሶ ግንባታና በአዲስ በመተካትና የትራንስፎርመሮችን አቅም በማሳደግ የኤሌክትሪክ ተደራሽነቱን ከዚህ በላይ ለማሳደግ እየሰራ ነው ብለዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ የአራት ሺህ ትራንስፎርመሮችን አቅም ማሳደግ እና ከ625 ኪሎ ሜትር በላይ ያረጁ መስመሮችንና ፖሎችን በአዲስ መቀየራቸውን ጠቅሰው፤ በክልሎችም ተመሳሳይ ሥራ በማከናወን የሀገሪቷ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽፋን 54 በመቶ ማድረስ እንደተቻለ ገልጸዋል፡፡
በ2018 በጀት ዓመትም ለ800 ሺህ ደንበኞች ቆጣሪ ለማሰራጨት እቅድ መያዙን ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የዜጎችን ፍትሐዊ የሀይል ተደራሽነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ጭምር እየተጠቀመ መሆኑንም አንስተዋል፡፡
በዚህም አገልግሎቱ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ማሳደግ የሚያስችል ዘመኑን የዋጅ "ስካዳ" የተሰኘ ቴክኖሎጂ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
"ስካዳ" በየትኛውም ቦታ የኤሌትሪክ ሃይል ሲቋረጥና ከመቋረጡ በፊት ቢሮ ውስጥ ሆኖ መቆጣጠር የሚያስችል ቴክኖሎጂ መሆኑን ገልጸው፤ የትኛው መስመር የትኛው ቦታ ላይ እንደተበላሸ ለማወቅ ያግዛል ብለዋል፡፡
ቴክኖሎጂው የኤሌትሪክ ሃይል እንዳይቆራረጥ ቀድሞ መረጃ በማጋራት ደንበኞች ከመደወላቸው በፊት ፈጣን ምላሽ መስጠት እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት የ"ስካዳ" ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በባህር ዳር፣ መቀሌ፣ ደሴ፣ ሐዋሳ፣ አዳማ፣ ድሬዳዋና ጅማ ተግባራዊ መሆኑን አመልክተው፤ በአዲስ አበባ ከተማም በአጭር ጊዜ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ እንደሚተገበር ተናግረዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026