የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ኤሌክትሪክ እንዳይቋረጥና ሲቋረጥም ፈጣን መረጃ የሚሰጥ "ስካዳ" የተሰኘ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተግባራዊ እየተደረገ ነው

Nov 10, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 30/2018(ኢዜአ)፦ ኤሌክትሪክ እንዳይቋረጥና ሲቋረጥም ፈጣን መረጃ በመስጠት የሃይል ተደራሽነትን ማስፋት የሚያስችል "ስካዳ" የተሰኘ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አንዋር አብራር ለኢዜአ እንዳሉት፤ የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት የዜጎችን የኑሮ ደረጃ በማሻሻልና የኢንዱስትሪ ልማትን በማስፋፋት ለኢኮኖሚያዊ ዕድገት ወሳኝ ነው፡፡

የለውጡ መንግስት አዳዲስ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማትን በማስፋፋት፣ ብዝኃ የሀይል ማመንጫዎችን በማስፋትና አዳዲስ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ፍትሐዊ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡

ያረጁ የኤሌክትሪክ መስመሮችን መልሶ ግንባታና በአዲስ በመተካትና የትራንስፎርመሮችን አቅም በማሳደግ የኤሌክትሪክ ተደራሽነቱን ከዚህ በላይ ለማሳደግ እየሰራ ነው ብለዋል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ የአራት ሺህ ትራንስፎርመሮችን አቅም ማሳደግ እና ከ625 ኪሎ ሜትር በላይ ያረጁ መስመሮችንና ፖሎችን በአዲስ መቀየራቸውን ጠቅሰው፤ በክልሎችም ተመሳሳይ ሥራ በማከናወን የሀገሪቷ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽፋን 54 በመቶ ማድረስ እንደተቻለ ገልጸዋል፡፡

በ2018 በጀት ዓመትም ለ800 ሺህ ደንበኞች ቆጣሪ ለማሰራጨት እቅድ መያዙን ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የዜጎችን ፍትሐዊ የሀይል ተደራሽነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ጭምር እየተጠቀመ መሆኑንም አንስተዋል፡፡

በዚህም አገልግሎቱ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ማሳደግ የሚያስችል ዘመኑን የዋጅ "ስካዳ" የተሰኘ ቴክኖሎጂ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

"ስካዳ" በየትኛውም ቦታ የኤሌትሪክ ሃይል ሲቋረጥና ከመቋረጡ በፊት ቢሮ ውስጥ ሆኖ መቆጣጠር የሚያስችል ቴክኖሎጂ መሆኑን ገልጸው፤ የትኛው መስመር የትኛው ቦታ ላይ እንደተበላሸ ለማወቅ ያግዛል ብለዋል፡፡

ቴክኖሎጂው የኤሌትሪክ ሃይል እንዳይቆራረጥ ቀድሞ መረጃ በማጋራት ደንበኞች ከመደወላቸው በፊት ፈጣን ምላሽ መስጠት እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት የ"ስካዳ" ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በባህር ዳር፣ መቀሌ፣ ደሴ፣ ሐዋሳ፣ አዳማ፣ ድሬዳዋና ጅማ ተግባራዊ መሆኑን አመልክተው፤ በአዲስ አበባ ከተማም በአጭር ጊዜ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ እንደሚተገበር ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026