የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በድሬዳዋ የሠራተኛውን የዲጂታል ክህሎት በማሳደግ ለተገልጋዮች ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ እየተሰራ ነው

Nov 13, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

የድሬዳዋ ፤ ህዳር 2/2018 (ኢዜአ)፡-በድሬዳዋ የሠራተኛውን የዲጂታል ክህሎት በማሳደግ ለተገልጋዮች ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ የማድረጉ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን የአስተዳደሩ የሲቪል ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ገለፀ ።

በድሬዳዋ በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የመንግስት ሠራተኛውን የቴክኖሎጂ ክህሎት ለማሳደግ በሚቻልበት አግባብ ላይ ቢሮው ከአስተዳደሩ የማዕከል ተቋማት የሰው ሃብት አመራሮች ጋር ዛሬ ተወያይቷል።


ውይይቱን የመሩት የቢሮው የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ የመሠረተ ልማት አቅርቦትና አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ኢማድ አብዱልቀዩም፤ በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና የሠራተኞችን የቴክኖሎጂ ክህሎት በማሳደግ የተገልጋዩን ፍላጎት ለማርካት እየተሰራ ነው።

የሠራተኛውን የቴክኖሎጂ ክህሎት ለማሳደግ ያልተቋረጠ ስልጠና እየሰጠ መሆኑንም አንስተዋል።

ስልጠናውም ዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ የመገንባት ጉዞን ለማሳካት ቁልፍ ሚና በመጫወቱ ሠራተኞች በእድሉ እንዲጠቀሙ ከተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንተናግረዋል ።

የተሰጠውን ስልጠና በአግባቡ የወሰዱ ሰራተኞች በየተቋማቸው ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመተግበር ለህዝቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ እያደረጉ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

እነዚህን አበረታች ስራዎች በላቀ መጠንና ፍጥነት ለማሳደግ የማዕከል ተቋማት የሰው ሃብት አመራሮች ተግተው መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል ።

በቀጣይም ተመሳሳይ ውይይት በሁሉም ተቋማት በማካሄድ ሠራተኛው የኢትዮ ኮደርስ ስልጠናው ተጠቃሚ እንዲሆን ይሰራል ብለዋል።

በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የድሬዳዋ አስተዳደር የፍትህ ፀጥታና የህግ ጉዳዮች ቢሮ የሰው ሃብት አመራር ዳይሬክተር ወይዘሮ ማሾ መሐመድ በበኩላቸው፤ ሠራተኞች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠናውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ሠራተኞች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠናን በአግባቡ በመውሰድ ተገልጋይን ለማርካት በሚደረገው የአሰራር ሂደት ለውጥ ማምጣት እንደሚገባቸው የገለጹት ደግሞ የአስተዳደሩ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ባለስልጣን የሰው ሃብት አመራር ዳይሬክተር ወይዘሮ ፌይሩዝ መሐመድ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026