🔇Unmute
ደሴ ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦አርሶ አደሩ ቀድሞ የደረሰን ሰብል ፈጥኖ በመሰብሰብ ወቅቱን ካልጠበቀ ዝናብ ከወዲሁ መከላከል እንደሚጠበቅበት በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የምስራቅ አማራ ሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል አሳሰበ።
በማዕከሉ የትንበያና ቅደመ ማስጠንቀቂያ ዴስክ ኃላፊ ሉባባ መሀመድ፤ ወቅቱ ደረቅ፣ ፀሐያማና ነፋሻማ ቢሆንም ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ እንደሚከሰት ትንበያዎች ያመለክታሉ ሲሉ ለኢዜአ ተናግረዋል።

ትንበያውን በመከተልም አርሶ አደሩ የደረሰ ሰበልን ፈጥኖ በመሰብሰብ ወቅቱን ካልጠበቀ ዝናብ ከወዲሁ እንዲከላከል አሳስበዋል።
የማዕከሉ የልማት ሚቲዎሮሎጂ ዴስክ ኃላፊ አቶ እንዳላማው ወንዴ በበኩላቸው፤ ከጥቅምት እስከ ጥር ባሉ የበጋ ወራት ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ ይጠበቃል ብለዋል።

አርሶ አደሩ የደረሰ ሰብል ከመሰብሰብ ጎን ለጎን ጎርፍን በዳር በማቆር ለመስኖ፣ ለቋሚ ተክልና ለእንስሳት ግጦሽ ልማት እንዲጠቀም መክረዋል።
በሌላ በኩል ጠዋትና ማታ ደግሞ ከፍተኛ ቅዝቃዜና ውርጭ ሊከሰት ስለሚችል ሕብረተሰቡ አለባበሱንና አመጋገቡን በማስተካከል እራሱን ከጉዳት እንዲጠብቅም መልዕክት አስተላልፈዋል።
በደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ይመር ሰይድ ፤ በዞኑ ቀድሞ የደረሰ ሰብል በወቅቱ እንዲሰበሰብ የተጠናከረ የባለሙያ ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል።

በዚህም እስካሁን በ32 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የለማ ጤፍ፣ ማሽላ፣ በቆሎ፣ ማሾና የጥራጥሬ ሰብል መሰብሰቡን አስታውቀዋል።
የሰብል መሰብሰብ ስራውን በአርሶ አደሩና በበጎፈቃደኞች ትብብር አጠናክሮ በማስቀጠል እስከ ታህሳስ አጋማሽ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገለጸዋል።

አርሶ አደሩ የሰበሰበውን ሰብል በጥንቃቄ እንዲከምርና በንፁህ አውድማ በመውቃት ለምርት ጥራት ትኩረት እንዲሰጥም መክረዋል።
በደቡብ ወሎ ዞን አጠቃላይ በመኸር ከለማው 432 ሺህ ሄክታር መሬት ከ15 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ከግብርና መምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026