🔇Unmute
ደሴ ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦አርሶ አደሩ ቀድሞ የደረሰን ሰብል ፈጥኖ በመሰብሰብ ወቅቱን ካልጠበቀ ዝናብ ከወዲሁ መከላከል እንደሚጠበቅበት በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የምስራቅ አማራ ሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል አሳሰበ።
በማዕከሉ የትንበያና ቅደመ ማስጠንቀቂያ ዴስክ ኃላፊ ሉባባ መሀመድ፤ ወቅቱ ደረቅ፣ ፀሐያማና ነፋሻማ ቢሆንም ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ እንደሚከሰት ትንበያዎች ያመለክታሉ ሲሉ ለኢዜአ ተናግረዋል።

ትንበያውን በመከተልም አርሶ አደሩ የደረሰ ሰበልን ፈጥኖ በመሰብሰብ ወቅቱን ካልጠበቀ ዝናብ ከወዲሁ እንዲከላከል አሳስበዋል።
የማዕከሉ የልማት ሚቲዎሮሎጂ ዴስክ ኃላፊ አቶ እንዳላማው ወንዴ በበኩላቸው፤ ከጥቅምት እስከ ጥር ባሉ የበጋ ወራት ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ ይጠበቃል ብለዋል።

አርሶ አደሩ የደረሰ ሰብል ከመሰብሰብ ጎን ለጎን ጎርፍን በዳር በማቆር ለመስኖ፣ ለቋሚ ተክልና ለእንስሳት ግጦሽ ልማት እንዲጠቀም መክረዋል።
በሌላ በኩል ጠዋትና ማታ ደግሞ ከፍተኛ ቅዝቃዜና ውርጭ ሊከሰት ስለሚችል ሕብረተሰቡ አለባበሱንና አመጋገቡን በማስተካከል እራሱን ከጉዳት እንዲጠብቅም መልዕክት አስተላልፈዋል።
በደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ይመር ሰይድ ፤ በዞኑ ቀድሞ የደረሰ ሰብል በወቅቱ እንዲሰበሰብ የተጠናከረ የባለሙያ ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል።

በዚህም እስካሁን በ32 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የለማ ጤፍ፣ ማሽላ፣ በቆሎ፣ ማሾና የጥራጥሬ ሰብል መሰብሰቡን አስታውቀዋል።
የሰብል መሰብሰብ ስራውን በአርሶ አደሩና በበጎፈቃደኞች ትብብር አጠናክሮ በማስቀጠል እስከ ታህሳስ አጋማሽ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገለጸዋል።

አርሶ አደሩ የሰበሰበውን ሰብል በጥንቃቄ እንዲከምርና በንፁህ አውድማ በመውቃት ለምርት ጥራት ትኩረት እንዲሰጥም መክረዋል።
በደቡብ ወሎ ዞን አጠቃላይ በመኸር ከለማው 432 ሺህ ሄክታር መሬት ከ15 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ከግብርና መምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026