🔇Unmute
ደሴ ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦አርሶ አደሩ ቀድሞ የደረሰን ሰብል ፈጥኖ በመሰብሰብ ወቅቱን ካልጠበቀ ዝናብ ከወዲሁ መከላከል እንደሚጠበቅበት በኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት የምስራቅ አማራ ሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ማዕከል አሳሰበ።
በማዕከሉ የትንበያና ቅደመ ማስጠንቀቂያ ዴስክ ኃላፊ ሉባባ መሀመድ፤ ወቅቱ ደረቅ፣ ፀሐያማና ነፋሻማ ቢሆንም ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ እንደሚከሰት ትንበያዎች ያመለክታሉ ሲሉ ለኢዜአ ተናግረዋል።

ትንበያውን በመከተልም አርሶ አደሩ የደረሰ ሰበልን ፈጥኖ በመሰብሰብ ወቅቱን ካልጠበቀ ዝናብ ከወዲሁ እንዲከላከል አሳስበዋል።
የማዕከሉ የልማት ሚቲዎሮሎጂ ዴስክ ኃላፊ አቶ እንዳላማው ወንዴ በበኩላቸው፤ ከጥቅምት እስከ ጥር ባሉ የበጋ ወራት ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ ይጠበቃል ብለዋል።

አርሶ አደሩ የደረሰ ሰብል ከመሰብሰብ ጎን ለጎን ጎርፍን በዳር በማቆር ለመስኖ፣ ለቋሚ ተክልና ለእንስሳት ግጦሽ ልማት እንዲጠቀም መክረዋል።
በሌላ በኩል ጠዋትና ማታ ደግሞ ከፍተኛ ቅዝቃዜና ውርጭ ሊከሰት ስለሚችል ሕብረተሰቡ አለባበሱንና አመጋገቡን በማስተካከል እራሱን ከጉዳት እንዲጠብቅም መልዕክት አስተላልፈዋል።
በደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ ይመር ሰይድ ፤ በዞኑ ቀድሞ የደረሰ ሰብል በወቅቱ እንዲሰበሰብ የተጠናከረ የባለሙያ ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል።

በዚህም እስካሁን በ32 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የለማ ጤፍ፣ ማሽላ፣ በቆሎ፣ ማሾና የጥራጥሬ ሰብል መሰብሰቡን አስታውቀዋል።
የሰብል መሰብሰብ ስራውን በአርሶ አደሩና በበጎፈቃደኞች ትብብር አጠናክሮ በማስቀጠል እስከ ታህሳስ አጋማሽ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገለጸዋል።

አርሶ አደሩ የሰበሰበውን ሰብል በጥንቃቄ እንዲከምርና በንፁህ አውድማ በመውቃት ለምርት ጥራት ትኩረት እንዲሰጥም መክረዋል።
በደቡብ ወሎ ዞን አጠቃላይ በመኸር ከለማው 432 ሺህ ሄክታር መሬት ከ15 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ከግብርና መምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025