🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በኢትዮጵያ የገንዘብ ማስተላለፍ አገልግሎት እንዲሰጡ የተፈቀደላቸውን የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶችን ስም ዝርዝር ለሕዝቡ ይፋ አድርጓል።
ባንኩ ለኢዜአ በላከው መግለጫ መሰረት ፣ ቀደም ሲል የገንዘብ ማስተላለፍ አገልግሎት እንዳይሰጥ ታግዶ የነበረውና ዋና መስሪያ ቤቱ በአሜሪካ ቪርጂኒያ ግዛት በፎልስ ቸርች የሚገኘው ራማዳ ፔይ (ካህ) በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ አጠቃላይ ግምገማ ከተካሄደ በኋላ በሕጋዊ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች ስም ዝርዝር ውስጥ ዳግም እንዲካተት መደረጉን ባንኩ በመግለጫው አመልክቷል።
ከዚህ ውሳኔ ላይ ሊደረስ የቻለው በሀገሪቱ ሕግና ደንብ መሠረት በድርጅቱ ላይ አስፈላጊው የቁጥጥርና የክትትል ሂደት ከተጠናቀቀ በኋላ መሆኑን ገልጿል።
በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ አገልግሎት እንዳይሰጡ ታግደው የሚገኙ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች በሙሉ የሀገሪቱ ሕግና ደንብ የሚጠይቀውን መስፈርት ለማሟላት አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስዱ አሳስቧል።
የብሔራዊ ባንክ ዓላማ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች በግልጽነትና ሕጉ በሚፈቅደው መሠረት ብቻ እንዲሠሩ ድጋፍ ማድረግ እንደሆነ ነው ያስታወቀው።
በውጭ አገር የሚኖሩ ሰዎች ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ በሚያስተላልፉበት በማንኛውም ወቅት ሕጋዊና ግልጽ የሆነ አካሄድ መከተላቸውን ማረጋገጥ እንደሚኖርባቸው አስገንዝቧል።
ሕጋዊ ፈቃድ በተሰጣቸው የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች በኩል ገንዘብ መላክ ገንዘቡ ደህንነቱ ተጠብቆና ሕገ ወጥ የገንዘብ ዝውውርንና አሸባሪነትን በገንዘብ መደገፍን የሚጻረረውን አሠራር ተከትሎ ወደ ተቀባዩ እንዲደርስ እንደሚያደርግ ነው በመግለጫው ያመለከተው።
ሕዝቡ ፈቃድ የተሰጣቸው የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶችን ለይቶ ለማወቅ ይችል ዘንድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሕጋዊ ድርጅቶችን ስም ዝርዝር በድረ ገጹhttps://nbe.gov.et/mta/ ይፋ ማድረጉን ባንኩ ጠቁሟል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሕጋዊ የሐዋላ አገልግሎትን ለማበረታታትና የፋይናንስ ዘርፍን ጤናማ ዕድገት ለመደገፍ የሚረዳ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ግልጽና ቀልጣፋ የፋይናንስ ምህዳር እንዲኖር በትጋት መሥራቱን እንደሚቀጥል አስታውቋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026