🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 14/2018(ኢዜአ)፦ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች የማስፋፋት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ገለጸ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ሚያዚያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም መርቀው ሥራ ማስጀመራቸው ይታወሳል።
በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ዜጎች ላይ ምሬት የሚፈጥሩ አሰራሮችን ፈትሾ ማስተካከል ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፥ ለዚህም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሁሉም አካባቢ እንደሚስፋፋ ገልጸው ነበር።

የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ(ዶ/ር)፥ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ልዩ ልዩ የመንግስት አገልግሎቶችን ዘመኑን በዋጀና በቴክኖሎጂ በተደገፈ መንገድ የሚሰጥበትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታትን ዓላማ ያደረገ ነው ብለዋል።
በመንግስት ተቋማት በሚሰጡ አገልግሎቶች የሚነሱ ቅሬታዎችን በጥራትና በፍጥነት ለመመለስ ፋይዳው የጎላ መሆኑንም ገልጸዋል።
የአገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተሰራበት እንደሚገኝም ተናግረዋል።
በዚህም እስከ ሚያዚያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ 75 የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከላት በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ወደ አገልግሎት ለማስገባት እየተሰራ ነው ብለዋል።
አገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋ ለማድረግ ብቁ የሰው ኃይል የማዘጋጀት፣ አገልግሎት የሚሰጥባቸውን ማዕከላት በቴክኖሎጂና በመሰረተ ልማት የማሟላት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የተጀመሩ ጥረቶች የሚበረታቱ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።
ኮሚሽኑም ለስራው ውጤታማነት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም በተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በዚህ ዓመት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎችን 100 ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን መናገራቸው ይታወቃል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026