የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች የማስፋፋት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል

Nov 24, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 14/2018(ኢዜአ)፦ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች የማስፋፋት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ገለጸ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ሚያዚያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም መርቀው ሥራ ማስጀመራቸው ይታወሳል።

በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ዜጎች ላይ ምሬት የሚፈጥሩ አሰራሮችን ፈትሾ ማስተካከል ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን ገልጸው፥ ለዚህም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በሁሉም አካባቢ እንደሚስፋፋ ገልጸው ነበር።


የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ(ዶ/ር)፥ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ልዩ ልዩ የመንግስት አገልግሎቶችን ዘመኑን በዋጀና በቴክኖሎጂ በተደገፈ መንገድ የሚሰጥበትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታትን ዓላማ ያደረገ ነው ብለዋል።

በመንግስት ተቋማት በሚሰጡ አገልግሎቶች የሚነሱ ቅሬታዎችን በጥራትና በፍጥነት ለመመለስ ፋይዳው የጎላ መሆኑንም ገልጸዋል።

የአገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተሰራበት እንደሚገኝም ተናግረዋል።

በዚህም እስከ ሚያዚያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ 75 የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከላት በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ወደ አገልግሎት ለማስገባት እየተሰራ ነው ብለዋል።

አገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋ ለማድረግ ብቁ የሰው ኃይል የማዘጋጀት፣ አገልግሎት የሚሰጥባቸውን ማዕከላት በቴክኖሎጂና በመሰረተ ልማት የማሟላት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የተጀመሩ ጥረቶች የሚበረታቱ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

ኮሚሽኑም ለስራው ውጤታማነት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም በተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በዚህ ዓመት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎችን 100 ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን መናገራቸው ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026