የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኢትዮጵያ ለተኪ ምርት የተሰጠው ትኩረት የምርታማነት አቅምን እያሳደገ ነው 

Nov 24, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 13/2018 (ኢዜአ)፡-በኢትዮጵያ ለተኪ ምርት የተሰጠው ትኩረት የኢንዱስትሪ ምርታማነት አቅማቸውን እያሳደገ እንደሚገኝ አምራች ኢንዱስትሪዎች ገለጹ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት ተግባራዊ የተደረገው ሀገር ሀቀፍ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪ ምርታማነትን በማነቃቃት ምቹ መደላድል እየፈጠረ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ታምርት ብሔራዊ ንቅናቄም የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ምርታማነትን በማሳደግ የሀገር ውስጥ ምርት ጥራትና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን በማሻሻል ለሀገር ዕድገት ገንቢ ሚና እንዲወጣ እያደረገ ነው።


በአምራች ኢንዱስትሪ ምርታማነት የተሰጠው ትኩረት ገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት ኢትዮጵያ የሚጠይቃትን የውጭ ምንዛሬን በማስቀረት በርካታ ዜጎችም የሥራ ዕድል እንዲፈጠርላቸው አድርጓል።

ከኢዜአ ቆይታ ያደረጉ በምግብና መጠጥ አምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማሩ ድርጅቶችም፤ መንግስት ለዘርፉ የሰጠው ትኩረት የኢንዱስትሪ ምርታማነት አቅምን በማሳደግ ምቹ ዕድሎችን ፈጥሯል ብለዋል።

በአዳማ ከተማ የሚገኘው የቱብራዘርስ የምግብ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አዩብ አረቦ፤ ለተኪ ምርት የተሰጠው ትኩረት የምርታማነት አቅማቸውን በማሳደግ ወሳኝ ሚና እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።


በኢትዮጵያ ለአምራች ኢንዱስትሪ የፈጠረው ምቹ መደላድልም ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት ከሀገር ውስጥ ገበያ አልፎ ለውጭ ገበያ ማቅረብ የሚችሉበትን ዕድል እየፈጠረ ነው ብለዋል።

የቱብራዘርስ የምግብ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ የፈጠረው የምርታማነት አቅም ከ3 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች በቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማስቻሉን ተናግረዋል።

በአዳማ ከተማ የአህዋን የምግብ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ የሰው ሃይል ልማትና አስተዳደር ዳይሬክተርና የፋብሪካው የቦርድ አማካሪ ጅብሪል አሰፋ፤ ፋብሪካው ከ500 በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥሯል ብለዋል።


በመንግስት ፖሊሲ መነሻነት በተኪ ምርት የውጭ ምንዛሬ የሚጠይቁ ጥራታቸውን የጠበቁ የፓስታና መኮሮኒ ምርቶችን በማምረት ለገበያ እያቀረቡ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በሸገር ከተማ አስተዳደር የፕሮማክሲዶር ኢትዮጵያ የምግብ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አማረ አበራ፤ መንግስት የአምራች ኢንዱስትሪ ምርታማነትን ለማሳደግ የማበረታቻ ድጋፍ እያደረገ ነው ብለዋል።


በዚህም የምርታማነት አቅማቸውን በማሳደግ ከሀገር ውስጥ ገበያ አልፎ ለውጭ ገበያ ማቅረብ የሚችሉበትን ዕድል እንደፈጠሩ ገልጸዋል።

በቱብራዘርስ የምግብ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ የሥራ ዕድል የተፈጠረለት ዳዊት መኮንን፤ የአምራች ኢንዱስትሪዎች መስፋፋት የዕውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግርን በማሳለጥ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እያደረጋቸው እንደሚገኝ ገልጿል።


በፋብሪካው የተፈጠረልኝ የሥራ ዕድል እራሴንና ቤተሰቤን የማስተዳድርበት ዕድል ተፈጥሮልኛል ያለችው ደግሞ የፕሮማክሲዶር ኢትዮጵያ የምግብ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ሠራተኛ ትብለጥ ከበደ ናት።


በአምራች ኢንዱስትሪ ልማት ኢኒስቲትዩት የምግብና መጠጥ ኢንዱስትሪ ምርምርና ልማት ማዕከል ሥራ አስኪያጅ ደበበ ወርቁ (ዶ/ር) የኢንዱስትሪ ምርታማነትን ለማበረታታት ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል።


የአምራች ኢንዱስትሪ ድጋፍና ክትትልም ዘርፉ የሚያጋጥመውን ተግዳሮት መፍትሔ በመስጠት የሀገር ውስጥ ተኪ ምርት አቅምን ማጎልበት እያስቻለ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026