የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በዞኑ የህዝቡን ተጠቃሚነት በላቀ ደረጃ የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው

Nov 26, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ወልቂጤ ፤ሕዳር 16/2018 (ኢዜአ)፦በጉራጌ ዞን የህዝቡን ተጠቃሚነት በላቀ ደረጃ የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑ ተገለጸ፡፡

በብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቅርንጫፍ 2ተኛ ዙር ሰልጣኝ አመራሮች በጉራጌ ዞን የተከናወኑ የልማት ስራዎችን ተመልክተዋል።

ሰልጣኝ አመራሮቹ በዞኑ የተከናወኑ የሌማት ትሩፋት፣ የግብርናና ኮሪደር ልማትን ጨምሮ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን የጎበኙ ሲሆን የተከናወኑ ተግባራት የህዝቡን ተጠቃሚነት በላቀ ደረጃ የሚያረጋግጡ ናቸው ብለዋል፡፡


ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ ሙሉቀን ገዙ፣ ወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ከመማር ማስተማር ስራው ጎን ለጎን የጀመራቸው ፕሮጀክቶች የህብረተሰቡን ጊዜ፣ ጉልበትንና በጀት የሚቀንሱ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

በተለይም በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የጀመራቸው ስራዎች የኑሮ ውድነትን ከማረጋጋት ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል የፈጠሩ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

ሌላኛው አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ አሰለፈች ለማ በበኩላቸው፤ በወልቂጤ ከተማ በሁሉም መስኮች እየተመዘገቡ የሚገኙ ስኬቶችን አድንቀዋል።

በየአካባቢው እየተሰሩ ያሉ ፕሮጀክቶች ጀምሮ የመጨረስ አቅም እያደገ ስለመምጣቱ ማሳያ ናቸው ያሉት ደግሞ አቶ በህሩ ኸይረዲን ናቸው።

ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል የፈጠሩ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍና የከተማ ግብርና ላይ ስኬታማ ስራዎች መመልከታቸውን ገልጸው የተጀመሩ ስራዎች ቀጣይነት እንዲኖራቸው አመራሩ ፍጥነት የታከለበት ስራ ማከናወን አለበት ብለዋል፡፡

የወልቂጤ ከተማ ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር፣ በከተማው የተጀመሩ የለውጡ ትሩፋቶች ለህዝቡ የልማት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡


በከተማው የውስጥ ለውስጥ አስፋልት መንገድ ግንባታ፣ የኮሪደር ልማት፣ ዘመናዊ የቄራ አገልግሎትና ሌሎችም መሰረተ ልማቶች በፍጥነት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በበኩላቸው፤ በዞኑ የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ሥራዎችን በላቀ ደረጃ ለመፈፀም በተሰራው ስራ አመርቂ ውጤት እየተመዘገበ ነው ብለዋል።


በዞኑ የሚከናወኑ የመሰረተ ልማት ስራዎች ፍጥነትንና ፈጠራን በማከል በውጤታማነት እየተተገበሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በዞኑ ያሉ አቅሞችን በመጠቀም በቱሪዝም፣ በግብርና ልማትና በሌሎች ሰው ተኮር የልማት ስራዎች ቀጣይነት ባለው ሁኔታ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አውስተዋል ፡፡

ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠል የሕዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በየደረጃው ያለው አመራር በሚወስደው ስልጠና የመፈጸምና የማስፈጸም አቅምን አጎልብቶ መቀጠል እንዳለበትም አሳስበዋል።

አመራሮቹ ባለፉት ቀናት የወሰዱት ስልጠና አቅማቸውና ክህሎታቸውን በማሳደግ በፍጥነት እና በጥራት የማስፈፀም አቅማቸውንም እንዳጎለበተውም ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025