🔇Unmute
ድሬዳዋ፤ ህዳር 19/2018(ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ የቱሪዝም ሀብቶችን ጠብቆና አልምቶ ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ይበልጥ ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ እንደሚገኙ የድረዳዋ አስተዳደር ባሕልና ቱሪዝም ጽህፈት ቤት ገለጸ።

የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ ወንደሰን አባይ እንደገለጹት፤ በዘርፉ በተከናወኑት በርካታ ተግባራት በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሶስት ወራት ከ291ሺህ በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ድሬዳዋን ጎብኝተዋል።
በአስተዳደሩ ስዕላዊ ጥበቦች ያሉባቸው የለገ ኦዳና ሌሎች ዋሻዎች እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ ከ10ኛው እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን የንግድ መተላለፊያ፣ የስልጣኔና የኃይማኖት ማዕከል በመሆን ያገለገለው ሐርላም የቱሪስቶች የስበት አምባ መሆኑን ለአብነት አንስተዋል።
እስካአሁን 56 ቅርሶች በሀገር አቀፍ ደረጃ ዕውቅና ተሰቷቸው መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ እነዚህን ሃብቶች ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ጋር በመቀናጀት በተገቢው መንገድ የመጠበቅ፣ የመንከባከብና የማስተዋወቅ ስራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
130 ዓመታት ላስቆጠረው የድሬዳዋ ምድር ባቡር ተርሚናል እና ለሐርላ የማሕበረሰብ ሙዚየም በኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ድጋፍ ዕድሳት ተደርጎላቸው ለቱሪስቶች ምቹ መደረጋቸውን አስታውሰዋል።

በተጨማሪም ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የዱር እንሰሳትና አእዋፋት መገኛ የሆነውን የቀላድ ጥብቅ ደን ምቹ የቱሪስት መዳረሻ እንዲሆን መሰራቱን ገልጸዋል።
በተቀናጀ መንገድ በትኩረት እየተሰሩ የሚገኙ ተግባራት የቱሪስት ፍሰትን በመጨመር ከዘርፉ የሚገኘውን ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች እያሳደገ ይገኛል ብለዋል።

በጽህፈት ቤቱ የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት 'ሬጉላቶሪ' ቡድን መሪ አቶ ሰይፈ ስጦታው በበኩላቸው፤ በዓመት ሁለት ጊዜ የሚከበረው የቁሉቢ ገብርኤል ንግስ በአል እና አመታዊ የድሬ ናፍቆት የዲያስፖራው ማሕበረሰብ በአልም ለቱሪስቶች መጨመር ጉልህ መደላደል መፍጠራቸውን ገልጸዋል።
በዚህም ከሐምሌ 2017ዓ.ም እስከ መስከረም 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ 129ሺህ 300 የሀገር ውስጥ እና 16ሺህ 750 የውጭ ቱሪስቶች ድሬዳዋን መጎብኘታቸውን አንስተዋል።
ከዚህም ከ1 ቢሊዮን 869 ሚሊዮን ብር በላይ በተዘዋዋሪ ገቢ መገኘቱንና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችም እንዲነቃቁ ማገዙን ተናግረዋል።
የኮሪደር ልማትን የመሳሰሉ ዘመናዊ መሠረተ ልማቶችና ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎች መገንባታቸው በቀጣይም ከቱሪዝም ዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ይበልጥ ለማሳደግ ያስችላሉ ነው ያሉት።
የአስተዳደሩ የቱሪዝም ሀብቶችን ጠብቆና ተንከባክቦ በማልማት ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ይበልጥ ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸወም ተገልጿል።
የቱሪዝም ሃብት ለአስተዳደሩ ሁለንተናዊ ዕድገት እና ለወጣቶች የስራ ዕድል መፍጠሪያ እንዲሆን ከምስራቅ ተጎራባች ክልሎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑም ተመልክቷል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025