የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የካዳስተር ቴክኖሎጂ ዘመናዊ የከተማ መሬት አስተዳደርና የውሳኔ አሰጣጥ አቅምን እያጎለበተ ነው - ሚኒስቴሩ

Dec 2, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 20/2018(ኢዜአ)፦ የካዳስተር ቴክኖሎጂ ዘመናዊ የከተማ መሬት አስተዳደርና የውሳኔ አሰጣጥ አቅምን እያሳደገ መሆኑን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ፈንታ ደጀን ገለጹ፡፡

ሚኒስትር ዴኤታው ለኢዜአ እንዳሉት፤ የካዳስተር መረጃ የከተሞችን የመሬት ሃብት በዘመናዊ አሰራር ሥርዓት ለመምራት ወሳኝ ነው፡፡

ባለፉት ሶስት ዓመታት ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የኢትዮጵያን የመሬት ገጽታ በካዳስተር ሥርዓት ማደራጀት የሚያስችል ስኬታማ ተግባር መከናወኑን ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ ከተሞች ወሰኑ በምድርና በካርታ ላይ በግልጽ ተለይቶ የመጠቀም መብት የተረጋገጠለት ልዩ የመለያ ኮድ ያለው ስድስት ነጥብ ስድስት ሚሊየን ቁራሽ መሬት ወይም ነጠላ የመሬት ይዞታ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

እስካሁንም በ150 ከተሞች ከሁለት ሚሊዮን በላይ ቁራሽ መሬት በካዳስተር ተመዝግቧል ብለዋል፡፡

የካዳስተር ቴክኖሎጂ መልክዓ-ምድራዊ የመረጃ ከተሞች ተዓማኒ፣ ትክክለኛና የተናበበ የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም እንዲኖራቸው እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

የካዳስተር ቴክኖሎጂ የከተማ መሬትን ለሚፈለገው የልማት ዓላማ እንዲውል በማስቻል የዜጎችን ፍትሕዊ የይዞታ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ማድረግ ያስችላል ብለዋል፡፡

የካዳስተር ቴክኖሎጂ ምዝገባ ሥርዓት በዕቅድ የሚመሩ ዘመናዊና የገቢ አቅማቸው ያደገ ከተሞች እንዲፈጠሩ እያደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።

በጥናት ላይ የተመሰረተ የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማት ግንባታዎችን በማሳለጥ የከተሞችን ዕድገት እያፋጠነ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።


በኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት የአየር ላይ ቅየሳ መሪ ሥራ አስፈፃሚ ከማሁ አብርሃም፤ የአየር ላይ ቅየሳ ቴክኖሎጂ በመጠቀም የኢትዮጵያ የመሬት ገጽታ በካዳስተር እንዲደራጅ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በካዳስተር የቴክኖሎጂ ሥርዓት የተደራጁ የመሬት ገጽታ መረጃዎችን ለውሳኔ ሰጪ አካላት እንዲቀረቡ እየተደረገ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም የመሬት ገጽታን በመለየት በአንድ ቋት መምራት የሚያስችል አቅም ይፈጥራል ብለዋል፡፡

በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ቀሪ የመሬት ገጽታዎችን በካዳስተር ቴክኖሎጂ ሥርዓት አደራጅቶ ለመያዝ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም አንስተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026