🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 21/2018 (ኢዜአ)፡- ችግር ገፍቶ የሚጥለን ሳይሆን ገፍቶ የሚያስፈነጥረን መሆን አለበት ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ “በመደመር መንግሥት ዕይታ የዘርፎች እመርታ” በሚል ርዕስ ለብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ስልጠና ሰጥተዋል።
በዚሁ ወቅትም፤ ችግሮች አሉ፤ ከዚያ ውስጥ መልካም ዕድሎችን ፈልቅቆ ማውጣት መቻል ይኖርብናል ብለዋል።
በችግር ትብታብ ታስረን እንዳንቀር ተስፈንጥረን ወደምንፈልገው ነገር እንድንደርስም በአንዳንድ ጉዳይ ላይ መደመራዊ ዝላይ አስፈላጊ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
የመደመር ዝላይ ትኩረት ግን አራት ጉዳዮች ላይ ማተኮር እንደሚጠበቅበትም ነው ያስረዱት።
እነሱም ሰው ተኮር ትውልድ መር መሆን፣ ብዝኃ ዘርፍ ሀገር አቀፍ መሆን፣ በምክክር ተግባብቶ ፖለቲካዊ ዕልባት ማምጣት እንዲሁም ዕውቀት ሸማች ብልጽግና አምራች መሆናቸውን አብራርተዋል።
ዱካ መከተል ቀላል ቢሆንም፤ ከሚፈለገው ግብ አንጻር በአጠረ ጊዜ ለመድረስ እንደማያስችልም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያነሱት።
መደመራዊ ዝላይ የሚያስፈልገው ክፍተትን (ጋፕን) ለመሙላት መሆኑን ጠቁመው፤ እመርታ ከመደመራዊ ዝላይ ውጭ ሊመጣ እንደማይችል አመላክተዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026