🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 21/2018 (ኢዜአ)፡- ችግር ገፍቶ የሚጥለን ሳይሆን ገፍቶ የሚያስፈነጥረን መሆን አለበት ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ “በመደመር መንግሥት ዕይታ የዘርፎች እመርታ” በሚል ርዕስ ለብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ስልጠና ሰጥተዋል።
በዚሁ ወቅትም፤ ችግሮች አሉ፤ ከዚያ ውስጥ መልካም ዕድሎችን ፈልቅቆ ማውጣት መቻል ይኖርብናል ብለዋል።
በችግር ትብታብ ታስረን እንዳንቀር ተስፈንጥረን ወደምንፈልገው ነገር እንድንደርስም በአንዳንድ ጉዳይ ላይ መደመራዊ ዝላይ አስፈላጊ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
የመደመር ዝላይ ትኩረት ግን አራት ጉዳዮች ላይ ማተኮር እንደሚጠበቅበትም ነው ያስረዱት።
እነሱም ሰው ተኮር ትውልድ መር መሆን፣ ብዝኃ ዘርፍ ሀገር አቀፍ መሆን፣ በምክክር ተግባብቶ ፖለቲካዊ ዕልባት ማምጣት እንዲሁም ዕውቀት ሸማች ብልጽግና አምራች መሆናቸውን አብራርተዋል።
ዱካ መከተል ቀላል ቢሆንም፤ ከሚፈለገው ግብ አንጻር በአጠረ ጊዜ ለመድረስ እንደማያስችልም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያነሱት።
መደመራዊ ዝላይ የሚያስፈልገው ክፍተትን (ጋፕን) ለመሙላት መሆኑን ጠቁመው፤ እመርታ ከመደመራዊ ዝላይ ውጭ ሊመጣ እንደማይችል አመላክተዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025