🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 21/2018 (ኢዜአ)፡- ችግር ገፍቶ የሚጥለን ሳይሆን ገፍቶ የሚያስፈነጥረን መሆን አለበት ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ “በመደመር መንግሥት ዕይታ የዘርፎች እመርታ” በሚል ርዕስ ለብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ስልጠና ሰጥተዋል።
በዚሁ ወቅትም፤ ችግሮች አሉ፤ ከዚያ ውስጥ መልካም ዕድሎችን ፈልቅቆ ማውጣት መቻል ይኖርብናል ብለዋል።
በችግር ትብታብ ታስረን እንዳንቀር ተስፈንጥረን ወደምንፈልገው ነገር እንድንደርስም በአንዳንድ ጉዳይ ላይ መደመራዊ ዝላይ አስፈላጊ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
የመደመር ዝላይ ትኩረት ግን አራት ጉዳዮች ላይ ማተኮር እንደሚጠበቅበትም ነው ያስረዱት።
እነሱም ሰው ተኮር ትውልድ መር መሆን፣ ብዝኃ ዘርፍ ሀገር አቀፍ መሆን፣ በምክክር ተግባብቶ ፖለቲካዊ ዕልባት ማምጣት እንዲሁም ዕውቀት ሸማች ብልጽግና አምራች መሆናቸውን አብራርተዋል።
ዱካ መከተል ቀላል ቢሆንም፤ ከሚፈለገው ግብ አንጻር በአጠረ ጊዜ ለመድረስ እንደማያስችልም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያነሱት።
መደመራዊ ዝላይ የሚያስፈልገው ክፍተትን (ጋፕን) ለመሙላት መሆኑን ጠቁመው፤ እመርታ ከመደመራዊ ዝላይ ውጭ ሊመጣ እንደማይችል አመላክተዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026