የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የገበያ ማዕከላቱ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ለገበያ መረጋጋት ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ነው

Dec 2, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ የተገነቡ ትላልቅ የገበያ ማዕከላት አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የገበያ መረጋጋትና ዘመናዊ የግብይት ሥርዓት በመፍጠር ጉልህ ሚና እየተጫወቱ መሆኑ ተገለጸ።

በአዲስ አበባ ከተማ የምርት ፍላጎትና አቅርቦትን በማመጣጠን የፍጆታ ምርቶችን በአንድ ቦታ ለመሸመት አማራጭ የግብይት ማዕከላት አለመኖር ተግዳሮት ሆኖ ቆይቷል።

የከተማ አስተዳደሩ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታትና የገበያውን ሁኔታ ለማረጋጋት የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰደ ሲሆን

ከእነዚህ ውስጥ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ የሚያገናኙ ግዙፍ የገበያ ማዕከላት ግንባታ አንዱ ነው።

በገበያ ማዕከላቱ የግብይት ሥርዓቱ ላይ የነበሩ የተንዛዙ አሰራሮችን ከማስቀረት ባለፈ ሸማቹ በተመጣጣኝ ዋጋ የሚፈልገውን ምርት እንዲያገኝ ዕድል ፈጥረዋል።

በከተማዋ መግቢያ በሮች የተገነቡ የገበያ ማዕከላት የምርት አቅርቦትና ፍላጎትን በማጣጣም ዘመናዊ የግብይት ሥርዓት መፍጠራቸውን ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ ሸማቾች፣ ነጋዴዎችና አምራቾች ተናግረዋል።


ሸማች ሙሉነሽ ደምሴ እና ዮሴፍ በቀለ በአቅራቢያቸው የተከፈቱ የገበያ ማዕከላት ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት እንዳስቻሏቸው ተናግረዋል።


በተለይም የፍጆታ ዕቃዎችን በአንድ ቦታ ላይ ማግኘት መቻላቸው ጊዜና ጉልበት እንደቆጠበላቸው በማንሳት።



በገበያ ማዕከላቱ ምርቶችን የሚያቀርቡ ነጋዴዎች በበኩላቸው ቀደም ሲል የነበረው የግብይት ሰንሰለት የተንዛዛና ለህገወጥነት የተጋለጠ መሆኑን አስታውሰዋል።



በገበያ ማዕከላቱ ከአምራቹ በቀጥታ የሚመጡ ምርቶችን ሸማቹን ማህበረሰብ ምርቶችንበተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ ማስቻሉን የተናገሩት ደግሞ ነጋዴ አበራሽ ወልደሩፋኤል እና ሀጂ ሁሴን የሱፍ ናቸው።


ከአምራቾች መካከል ጉርሜሳ ጀልቀባ በገበያ ማዕከላቱ የግብይት እሴት ሰንሰለቱ እንዲያጥር በመደረጉ የተረጋጋ የምርቶች ዋጋ እንዲኖር አስችሏል ነው ያሉት።


የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ሀቢባ ሲራጅ በበኩላቸው በከተማዋ የነበሩ አላስፈላጊ የግብይት ሰብሰለቶችን በማስወገድ በከተማዋ መግቢያ በሮች ላይ አምስት ትላልቅ የገበያ ማዕከላት መገንባታቸውን አንስተዋል።

ማዕከላቱ አላስፈላጊ የንግድ ሰንሰለትን በማሳጠር አምራቹን ነጋዴውንና ሸማቹን በቀጥታ እንዲገናኙ አድርገዋል ነው ያሉት።

ከዚህ ባለፈ በአራት የግብይት ቦታዎች የተጀመረው የቅዳሜና እሁድ ገበያ አሁን ላይ ወደ 219 ከፍ ማለቱ ለገበያ መረጋጋት ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል።

በአዲስ አበባ መግቢያ በሮች የተገነቡት 5ቱ ዘመናዊ የገበያ ማዕከላት ላፍቶ ሁለገብ የገበያ ማዕከል ቁጥር 1፣ ላፍቶ ሁለገብ ገበያ ማዕከል ቁጥር 2 (ዘመናዊ ሀይፐር ማርኬት እና ሁሉንም የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርች ወዘተ በአንድ ማዕከል ያየዘ)፣ ለሚ ኩራ የገብርና ምርቶች የገበያ ማዕከል፣ ኮልፌ የገብርና ምርቶች የገበያ ማዕከል፣ አቃቂ ቃሊቲ የገብርና ምርቶች የገበያ ማዕከላት ናቸው።

የገበያ ማዕከላቱ ዘመናዊ የግብይት ስርዓት እንዲኖር በማድረግ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ፍትሃዊ የግብይት ስርዓት እንዲሰፍን እያስቻሉም ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026