የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የገበያ ማዕከላቱ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ለገበያ መረጋጋት ጉልህ ሚና እየተጫወቱ ነው

Dec 2, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ የተገነቡ ትላልቅ የገበያ ማዕከላት አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የገበያ መረጋጋትና ዘመናዊ የግብይት ሥርዓት በመፍጠር ጉልህ ሚና እየተጫወቱ መሆኑ ተገለጸ።

በአዲስ አበባ ከተማ የምርት ፍላጎትና አቅርቦትን በማመጣጠን የፍጆታ ምርቶችን በአንድ ቦታ ለመሸመት አማራጭ የግብይት ማዕከላት አለመኖር ተግዳሮት ሆኖ ቆይቷል።

የከተማ አስተዳደሩ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመፍታትና የገበያውን ሁኔታ ለማረጋጋት የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰደ ሲሆን

ከእነዚህ ውስጥ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ የሚያገናኙ ግዙፍ የገበያ ማዕከላት ግንባታ አንዱ ነው።

በገበያ ማዕከላቱ የግብይት ሥርዓቱ ላይ የነበሩ የተንዛዙ አሰራሮችን ከማስቀረት ባለፈ ሸማቹ በተመጣጣኝ ዋጋ የሚፈልገውን ምርት እንዲያገኝ ዕድል ፈጥረዋል።

በከተማዋ መግቢያ በሮች የተገነቡ የገበያ ማዕከላት የምርት አቅርቦትና ፍላጎትን በማጣጣም ዘመናዊ የግብይት ሥርዓት መፍጠራቸውን ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ ሸማቾች፣ ነጋዴዎችና አምራቾች ተናግረዋል።


ሸማች ሙሉነሽ ደምሴ እና ዮሴፍ በቀለ በአቅራቢያቸው የተከፈቱ የገበያ ማዕከላት ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት እንዳስቻሏቸው ተናግረዋል።


በተለይም የፍጆታ ዕቃዎችን በአንድ ቦታ ላይ ማግኘት መቻላቸው ጊዜና ጉልበት እንደቆጠበላቸው በማንሳት።



በገበያ ማዕከላቱ ምርቶችን የሚያቀርቡ ነጋዴዎች በበኩላቸው ቀደም ሲል የነበረው የግብይት ሰንሰለት የተንዛዛና ለህገወጥነት የተጋለጠ መሆኑን አስታውሰዋል።



በገበያ ማዕከላቱ ከአምራቹ በቀጥታ የሚመጡ ምርቶችን ሸማቹን ማህበረሰብ ምርቶችንበተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ ማስቻሉን የተናገሩት ደግሞ ነጋዴ አበራሽ ወልደሩፋኤል እና ሀጂ ሁሴን የሱፍ ናቸው።


ከአምራቾች መካከል ጉርሜሳ ጀልቀባ በገበያ ማዕከላቱ የግብይት እሴት ሰንሰለቱ እንዲያጥር በመደረጉ የተረጋጋ የምርቶች ዋጋ እንዲኖር አስችሏል ነው ያሉት።


የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ሀቢባ ሲራጅ በበኩላቸው በከተማዋ የነበሩ አላስፈላጊ የግብይት ሰብሰለቶችን በማስወገድ በከተማዋ መግቢያ በሮች ላይ አምስት ትላልቅ የገበያ ማዕከላት መገንባታቸውን አንስተዋል።

ማዕከላቱ አላስፈላጊ የንግድ ሰንሰለትን በማሳጠር አምራቹን ነጋዴውንና ሸማቹን በቀጥታ እንዲገናኙ አድርገዋል ነው ያሉት።

ከዚህ ባለፈ በአራት የግብይት ቦታዎች የተጀመረው የቅዳሜና እሁድ ገበያ አሁን ላይ ወደ 219 ከፍ ማለቱ ለገበያ መረጋጋት ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል።

በአዲስ አበባ መግቢያ በሮች የተገነቡት 5ቱ ዘመናዊ የገበያ ማዕከላት ላፍቶ ሁለገብ የገበያ ማዕከል ቁጥር 1፣ ላፍቶ ሁለገብ ገበያ ማዕከል ቁጥር 2 (ዘመናዊ ሀይፐር ማርኬት እና ሁሉንም የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርች ወዘተ በአንድ ማዕከል ያየዘ)፣ ለሚ ኩራ የገብርና ምርቶች የገበያ ማዕከል፣ ኮልፌ የገብርና ምርቶች የገበያ ማዕከል፣ አቃቂ ቃሊቲ የገብርና ምርቶች የገበያ ማዕከላት ናቸው።

የገበያ ማዕከላቱ ዘመናዊ የግብይት ስርዓት እንዲኖር በማድረግ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት ፍትሃዊ የግብይት ስርዓት እንዲሰፍን እያስቻሉም ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026