🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ)፦ በመደመር መንግሥት ዕይታ የገጠር ሽግግርን ለማረጋገጥ ውጤታማ የፖሊሲ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለሰ መኮንን(ዶ/ር) ገለጹ።
የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት "የገጠር ትራንስፎርሜሽንን በማሳደግ ውጤታማና ባለብዙ ዘርፍ የትብብር ተፅዕኖን ማጎልበት" በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጀው የፓናል ውይይት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለሰ መኮንን(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ መንግሥት የገጠር ሽግግርን በማፋጠን የአርሶ አደሩንና አርብቶ አደሩን ሕይወት ለማሻሻል እየሰራ ነው።
በመደመር መንግሥት ዕይታ የገጠር ትራንስፎርሜሽንን ለማረጋገጥ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችም ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የገጠሩን የህብረተሰብ ክፍል ኑሮ ማሻሻል አካታች ልማትና ዕድገትን የማረጋገጥ እንዲሁም ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ የማሳደግ ጉዳይ በመሆኑ የግብርና ትራንስፎርሜሽንን ማፋጠን ትኩረት ተሰጥቶታል ነው ያሉት።
የገጠር ሽግግርን ለማፋጠን ባለድርሻ አካላት ቅንጅትና ትብብራቸውን በመደመር እሳቤ የበለጠ ማጠናከር እንዳለባቸውም አንስተዋል።
የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የኩታ ገጠም እርሻን በማስፋፋት የገጠር ትራንስፎርሜሽንን ለማረጋገጥ እየሰራች ነው ብለዋል።

ገበያ-ተኮር የግብርና ምርቶችን በብዛትና በጥራት በማምረት አርሶ አደሩ ተጠቃሚ የሚሆንባቸው አሰራሮች እየተተገበሩ እንደሚገኙም ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ የ10 ዓመት የገጠር ትራንስፎርሜሽን ፖሊሲ ውጤታማ እንዲሆን የባለድርሻ አካላት ትብብር ወሳኝ ነው ብለዋል።
በመድረኩ የመንግሥት አመራሮች፣ የፖሊሲ አውጪዎች፣ የግብርና ዘርፍ ባለሙያዎችና ተመራማሪዎች እንዲሁም የልማት አጋሮች የተገኙ ሲሆን፥ የገጠር ሽግግር ላይ ያተኮሩ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች እንደሚቀርቡ እንዲሁም በኢትዮጵያ የገጠር ሽግግርን ለማምጣት ያሉ ዕድሎችና ተግዳሮቶች ላይ ባለድርሻ አካላት ምክክር ያደርጋሉ ተብሏል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026