የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በመደመር መንግሥት ዕይታ የገጠር ሽግግርን ለማረጋገጥ  ውጤታማ  የፖሊሲ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው

Dec 2, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ)፦ በመደመር መንግሥት ዕይታ የገጠር ሽግግርን ለማረጋገጥ ውጤታማ የፖሊሲ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለሰ መኮንን(ዶ/ር) ገለጹ።

የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት "የገጠር ትራንስፎርሜሽንን በማሳደግ ውጤታማና ባለብዙ ዘርፍ የትብብር ተፅዕኖን ማጎልበት" በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጀው የፓናል ውይይት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።


የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለሰ መኮንን(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ መንግሥት የገጠር ሽግግርን በማፋጠን የአርሶ አደሩንና አርብቶ አደሩን ሕይወት ለማሻሻል እየሰራ ነው።

በመደመር መንግሥት ዕይታ የገጠር ትራንስፎርሜሽንን ለማረጋገጥ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎችም ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የገጠሩን የህብረተሰብ ክፍል ኑሮ ማሻሻል አካታች ልማትና ዕድገትን የማረጋገጥ እንዲሁም ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ የማሳደግ ጉዳይ በመሆኑ የግብርና ትራንስፎርሜሽንን ማፋጠን ትኩረት ተሰጥቶታል ነው ያሉት።

የገጠር ሽግግርን ለማፋጠን ባለድርሻ አካላት ቅንጅትና ትብብራቸውን በመደመር እሳቤ የበለጠ ማጠናከር እንዳለባቸውም አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የኩታ ገጠም እርሻን በማስፋፋት የገጠር ትራንስፎርሜሽንን ለማረጋገጥ እየሰራች ነው ብለዋል።


ገበያ-ተኮር የግብርና ምርቶችን በብዛትና በጥራት በማምረት አርሶ አደሩ ተጠቃሚ የሚሆንባቸው አሰራሮች እየተተገበሩ እንደሚገኙም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ የ10 ዓመት የገጠር ትራንስፎርሜሽን ፖሊሲ ውጤታማ እንዲሆን የባለድርሻ አካላት ትብብር ወሳኝ ነው ብለዋል።

በመድረኩ የመንግሥት አመራሮች፣ የፖሊሲ አውጪዎች፣ የግብርና ዘርፍ ባለሙያዎችና ተመራማሪዎች እንዲሁም የልማት አጋሮች የተገኙ ሲሆን፥ የገጠር ሽግግር ላይ ያተኮሩ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች እንደሚቀርቡ እንዲሁም በኢትዮጵያ የገጠር ሽግግርን ለማምጣት ያሉ ዕድሎችና ተግዳሮቶች ላይ ባለድርሻ አካላት ምክክር ያደርጋሉ ተብሏል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025