የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ከለውጡ መንግሥት በኋላ በሶማሌ ክልል የግብርናው ዘርፍ እመርታዊ ውጤት አምጥቷል

Dec 2, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ)፡-ከለውጡ መንግሥት በኋላ የግብርናው ዘርፍ አስደናቂ ለውጥ ማምጣቱን የሶማሌ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ምክትል ኃላፊ አሕመድኑር አብዲ ለኢዜአ እንዳሉት፤ እንደ ክልል ከለውጡ መንግሥት በፊት ሲታረስ የነበረው መሬት 389 ሺህ 949 ሔክታር ነው።

የለውጡ መንግሥት ለክልሉ በሰጠው ልዩ ትኩረት በአሁኑ ወቅት 1 ሚሊየን 585 ሺህ 889 ሔክታር መሬት እየለማ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ይህ የለውጡ መንግሥት ትጋት ቀደም ሲል ክልሉ ለአርብቶ አደር እንጅ ለግብርና ሥራ እንደማይሆን የተተከለውን ትርክት በተግባር ያፈረሰ ነው ብለዋል።


በዚህ ሂደትም አሁን ላይ እንደ ክልል 971 ሺህ 430 አባዎራዎችን በግብርና ልማት ብቻ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ነው ያነሱት።

ምንም እንኳን እንደ ሰብሉ ዓይነት ቢለያይም በአሁኑ ወቅት በአማካይ በሔክታር 40 ኩንታል እንደሚመረት ጠቁመዋል።

መልማት የሚችል መሬት እያለን በሚፈለገው ልክ በማልማት ተጠቃሚ ሳንሆን መቆየታችን ቢያስቆጭም፤ አሁን ማካካስ ተችሏል ሲሉ ገልጸዋል።


የለውጡ መንግሥት በቅድሚያ የአካባቢውን ሰላም ማስጠበቅ መቻሉ እና ሕዝቡ ተረጋግቶ ፊቱን ወደ ልማት እንዲያዞር በማድረጉ ሰፊ መሬት ለማልማት ተችሏል ነው ያሉት።

ከአርብቶ አደርነት ጎን ለጎን የእርሻ ሥራዎችንም በስፋት በማከናወን ሕዝቡን በይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ መሠራቱ የሚለማውን መሬት መጠን እንዳሳደገው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026