የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኢትዮጵያ የሠራተኛ ማኅበራት የሠራተኞችን አቅም በማጎልበት ለብሔራዊ የምርታማነት ዕድገት ሚናውን ሊወጣ ይገባል

Dec 3, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 23/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን የሠራተኞችን አቅም በማጎልበት ለብሔራዊ የምርታማነት ዕድገት ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለጹ።

የዓለም አቀፉ የሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ስብሰባ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።


በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝደንት አደም ፋራህ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ዓለም አቀፍ ግጭቶች፣ የኢኮኖሚ መናጋት፣ የአየር ንብረት ለውጥና የቴክኖሎጂ መስተጓጎል በሥራ ከባቢ ላይ ጫና እያሳደሩ ነው።

በዚህ በተለዋዋጭ የዓለም ሁኔታ የትምህርትና ቴክኖሎጂ ተደራሽነትን በማስፋትና በአዳዲስ የኢንቨስትመንት ፍሰት የዜጎችን ሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ለተቋማት ግንባታ የተሰጠው ትኩረት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማሳደግ ውጤት እያስመዘገበ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

በተለይም የክህሎት ልማትን በማጠናከርና ምቹ የሥራ ምህዳር በመፍጠር በርካታ ወጣቶችና ሴቶችን በማብቃት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን አብራርተዋል።


የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገትና የሥራ ስምሪት የሠራተኞችን መብት የሚያስጠበቅ ምቹ ምኅዳር እንዲፈጠር ማስቻሉን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት በመንግስት የሪፎርም ሥራዎች ስኬት ወሳኝ አጋር ሆነው መቀጠላቸውንም አንስተዋል።

በቀጣይም ፈጠራን በማበረታታትና ብቁ የሰው ኃይል ግንባታን በማጠናከር የብሔራዊ የምርታማነት አቅም የማሳደግ ጉዞ ላይ አሻራቸውን ሊያሳርፉ እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል።

የመንግሥት፣ የሠራተኛ ኮንፌዴሬሽኖችና አሠሪ ማኅበራት ግንኙነትም በመተማመን፣ ግልጽነትና የጋራ ተሳትፎ ላይ የተመሠረተ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ የሠራተኞችን ክብርና መብት በመጠበቅ በዓለም አቀፍ ስምምነቶች መሠረት ለተሻለ የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት አበክራ እየሠራች መሆኗንም አቶ አደም ፋራህ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026