🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 23/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን የሠራተኞችን አቅም በማጎልበት ለብሔራዊ የምርታማነት ዕድገት ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለጹ።
የዓለም አቀፉ የሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ስብሰባ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝደንት አደም ፋራህ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ዓለም አቀፍ ግጭቶች፣ የኢኮኖሚ መናጋት፣ የአየር ንብረት ለውጥና የቴክኖሎጂ መስተጓጎል በሥራ ከባቢ ላይ ጫና እያሳደሩ ነው።
በዚህ በተለዋዋጭ የዓለም ሁኔታ የትምህርትና ቴክኖሎጂ ተደራሽነትን በማስፋትና በአዳዲስ የኢንቨስትመንት ፍሰት የዜጎችን ሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ለተቋማት ግንባታ የተሰጠው ትኩረት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማሳደግ ውጤት እያስመዘገበ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በተለይም የክህሎት ልማትን በማጠናከርና ምቹ የሥራ ምህዳር በመፍጠር በርካታ ወጣቶችና ሴቶችን በማብቃት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገትና የሥራ ስምሪት የሠራተኞችን መብት የሚያስጠበቅ ምቹ ምኅዳር እንዲፈጠር ማስቻሉን አስረድተዋል።
የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት በመንግስት የሪፎርም ሥራዎች ስኬት ወሳኝ አጋር ሆነው መቀጠላቸውንም አንስተዋል።
በቀጣይም ፈጠራን በማበረታታትና ብቁ የሰው ኃይል ግንባታን በማጠናከር የብሔራዊ የምርታማነት አቅም የማሳደግ ጉዞ ላይ አሻራቸውን ሊያሳርፉ እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል።
የመንግሥት፣ የሠራተኛ ኮንፌዴሬሽኖችና አሠሪ ማኅበራት ግንኙነትም በመተማመን፣ ግልጽነትና የጋራ ተሳትፎ ላይ የተመሠረተ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የሠራተኞችን ክብርና መብት በመጠበቅ በዓለም አቀፍ ስምምነቶች መሠረት ለተሻለ የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት አበክራ እየሠራች መሆኗንም አቶ አደም ፋራህ ተናግረዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026