🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 23/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን የሠራተኞችን አቅም በማጎልበት ለብሔራዊ የምርታማነት ዕድገት ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለጹ።
የዓለም አቀፉ የሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ስብሰባ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝደንት አደም ፋራህ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ዓለም አቀፍ ግጭቶች፣ የኢኮኖሚ መናጋት፣ የአየር ንብረት ለውጥና የቴክኖሎጂ መስተጓጎል በሥራ ከባቢ ላይ ጫና እያሳደሩ ነው።
በዚህ በተለዋዋጭ የዓለም ሁኔታ የትምህርትና ቴክኖሎጂ ተደራሽነትን በማስፋትና በአዳዲስ የኢንቨስትመንት ፍሰት የዜጎችን ሥራ ዕድል ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ለተቋማት ግንባታ የተሰጠው ትኩረት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማሳደግ ውጤት እያስመዘገበ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በተለይም የክህሎት ልማትን በማጠናከርና ምቹ የሥራ ምህዳር በመፍጠር በርካታ ወጣቶችና ሴቶችን በማብቃት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገትና የሥራ ስምሪት የሠራተኞችን መብት የሚያስጠበቅ ምቹ ምኅዳር እንዲፈጠር ማስቻሉን አስረድተዋል።
የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት በመንግስት የሪፎርም ሥራዎች ስኬት ወሳኝ አጋር ሆነው መቀጠላቸውንም አንስተዋል።
በቀጣይም ፈጠራን በማበረታታትና ብቁ የሰው ኃይል ግንባታን በማጠናከር የብሔራዊ የምርታማነት አቅም የማሳደግ ጉዞ ላይ አሻራቸውን ሊያሳርፉ እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል።
የመንግሥት፣ የሠራተኛ ኮንፌዴሬሽኖችና አሠሪ ማኅበራት ግንኙነትም በመተማመን፣ ግልጽነትና የጋራ ተሳትፎ ላይ የተመሠረተ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የሠራተኞችን ክብርና መብት በመጠበቅ በዓለም አቀፍ ስምምነቶች መሠረት ለተሻለ የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት አበክራ እየሠራች መሆኗንም አቶ አደም ፋራህ ተናግረዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025