🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 27/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ፍላጎቶች የሚያሳኩ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ቀና የሚያደርጓት የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑ ተገለፀ፡፡
''የጉባ ብስራቶች፤ የመደመር መንግሥት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ሕዝባዊ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስራ እና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ ሚሊዮን ማቲዎስ የመወያያ ሰነድ አቅርበዋል።
በቦሌ ክፍለ ከተማ በተካሄደው ህዝባዊ የውይይት መድረክ ላይ መንግስት የከተማዋን ብልፅግና እውን ለማድረግ የጀመረው ጉዞ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ቀርቧል።
በቦሌ ክፍለ ከተማ በነበረው ህዝባዊ የውይይት መድረክ ላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የወከሉ ነዋሪዎች በተሰሩ የልማት ስራዎችና መሰራት በሚገቡ ጉዳዮች ዙሪያ ከመንግስት ከፍተኛ ኃላፊዎች ጋር መክረዋል።
ነዋሪዎቹ በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ከተማዋን የቀየሩ እና የረጀም ጊዜ ችግሮችን የፈቱ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የከተማዋ የውሃ አቅርቦት ሁኔታ በውይይት መድረኩ ላይ ከተነሱት እና ምላሽ ካገኙ ጥያቄዎች መካከል ይገኝበታል።
የቤት አቀርቦት አሁን የከተማዋ ችግር ቢሆንም ከተማ አስተዳደሩ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመቶ ሺዎች የሚቆጡ ቤቶችን ገንብቶ ማስተላለፉ ተመላክቷል።
ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተገናኘ አሁንም ችግሮች መኖራቸውን ነዋሪዎቹ ያነሱ ሲሆን ከተማ አስተዳደሩ ችግሩን ለመፍታት ዘርፈ ብዙ እርምጃዎችን እየወሰደ እንደሚገኝም ተገልጿል።
ውይይቱን የመሩት የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትሩ አብርሃም በላይ(ዶ/ር) የብልፅግና ፓርቲ ዋነኛ አጀንዳ ለትውልድ የሚተላለፉ ልማቶችን ሰርቶ ማለፍ መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም የጉባ ብስራቶችን ባስቀመጥነው ጊዜ ፈጽመን የኢትዮጵያን ማንሰራራት ለማረጋገጥ እንሰራለን ሲሉም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያን ፍላጎቶች የሚያሳኩ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ቀና የሚያደርጓት የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ያብራሩት ደግሞ የብልፅግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) ናቸው።
በብዙ መንገድ አሁን ላይ ኢትዮጵያ በመነቃቃት ላይ ትገኛለች ለዚህም ለችግር የማይበገር ኢኮኖሚ እየተገነባ መሆኑንም ገልጸዋል።
በቦሌ ክፍለ ከተማ በነበረው ህዝባዊ የውይይት መድረክ ላይ መንግስት የከተማዋን ብልፅግና እውን ለማድረግ የጀመረው የልማት ጉዞ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025