🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 27/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ፍላጎቶች የሚያሳኩ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ቀና የሚያደርጓት የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑ ተገለፀ፡፡
''የጉባ ብስራቶች፤ የመደመር መንግሥት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ሕዝባዊ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስራ እና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ ሚሊዮን ማቲዎስ የመወያያ ሰነድ አቅርበዋል።
በቦሌ ክፍለ ከተማ በተካሄደው ህዝባዊ የውይይት መድረክ ላይ መንግስት የከተማዋን ብልፅግና እውን ለማድረግ የጀመረው ጉዞ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ቀርቧል።
በቦሌ ክፍለ ከተማ በነበረው ህዝባዊ የውይይት መድረክ ላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የወከሉ ነዋሪዎች በተሰሩ የልማት ስራዎችና መሰራት በሚገቡ ጉዳዮች ዙሪያ ከመንግስት ከፍተኛ ኃላፊዎች ጋር መክረዋል።
ነዋሪዎቹ በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑ የልማት ስራዎች ከተማዋን የቀየሩ እና የረጀም ጊዜ ችግሮችን የፈቱ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የከተማዋ የውሃ አቅርቦት ሁኔታ በውይይት መድረኩ ላይ ከተነሱት እና ምላሽ ካገኙ ጥያቄዎች መካከል ይገኝበታል።
የቤት አቀርቦት አሁን የከተማዋ ችግር ቢሆንም ከተማ አስተዳደሩ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመቶ ሺዎች የሚቆጡ ቤቶችን ገንብቶ ማስተላለፉ ተመላክቷል።
ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተገናኘ አሁንም ችግሮች መኖራቸውን ነዋሪዎቹ ያነሱ ሲሆን ከተማ አስተዳደሩ ችግሩን ለመፍታት ዘርፈ ብዙ እርምጃዎችን እየወሰደ እንደሚገኝም ተገልጿል።
ውይይቱን የመሩት የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትሩ አብርሃም በላይ(ዶ/ር) የብልፅግና ፓርቲ ዋነኛ አጀንዳ ለትውልድ የሚተላለፉ ልማቶችን ሰርቶ ማለፍ መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም የጉባ ብስራቶችን ባስቀመጥነው ጊዜ ፈጽመን የኢትዮጵያን ማንሰራራት ለማረጋገጥ እንሰራለን ሲሉም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያን ፍላጎቶች የሚያሳኩ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ቀና የሚያደርጓት የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ያብራሩት ደግሞ የብልፅግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) ናቸው።
በብዙ መንገድ አሁን ላይ ኢትዮጵያ በመነቃቃት ላይ ትገኛለች ለዚህም ለችግር የማይበገር ኢኮኖሚ እየተገነባ መሆኑንም ገልጸዋል።
በቦሌ ክፍለ ከተማ በነበረው ህዝባዊ የውይይት መድረክ ላይ መንግስት የከተማዋን ብልፅግና እውን ለማድረግ የጀመረው የልማት ጉዞ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026