🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 27/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወኑ ያሉ ትልልቅ የልማት ፕሮጀክቶች የህዝብ እና የመንግስት ቅንጅት ውጤት መሆናቸውን በየካ ክፍለ ከተማ በተካሄደው ህዝባዊ ውይይት ላይ የተሳተፉ ነዋሪዎች ተናገሩ።
በአዲስ አበባ በሁሉም ክፍለ ከተሞች "የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግሥት ትሩፋቶች" በሚል ሀሳብ ህዝባዊ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።
በአዲስ አበባ ከተማም ሆነ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተሰሩ ያሉ ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶች የህዝብ እና የመንግስት ቅንጅት ውጤት መሆናቸውን በየካ ክፍለ ከተማ በተካሄደው ህዝባዊ ውይይት የተሳተፉ የህበረተሰብ ክፍሎች ተናግረዋል።

ነዋሪዎቹ ሀገርን የማበልፀግ ርዕይ የሚጨበጥ ውጤት እንዲመዘገብ ማስቻሉንም ጠቅሰዋል።
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ከተማ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ሞገስ ባልቻ በመድረኩ ላይ እንዳሉት በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶች የለውጡ መንግስት የህዝብ ኃብትን በተገቢው መንገድ በመጠቀም የልማት ስራዎችን በፍጥነት እና በጥራት ማከናወን በመቻሉ የመጣ ስኬት ነው ብለዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ ለዘመናት ያልተሰሩ ውዝፍ ስራዎችን በሁሉም ዘርፍ ለመስራት ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ በበኩላቸው ከተሞችን ለመለወጥ በሚደረገው ጥረት የነዋሪው ሚና ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል።
ኢትዮጵያ በጉባ ብስራቶች ይፋ ያደረገቻቸው ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ሀገርን የማበልፀግ ርዕይን እውን እንደሚያደርጉ ያብራሩት ደግሞ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ(ዶ/ር) ናቸው።
በየካ ክፍለ ከተማ ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር በተደረገው ዉይይት ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025