🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 27/2018(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወኑ ያሉ ትልልቅ የልማት ፕሮጀክቶች የህዝብ እና የመንግስት ቅንጅት ውጤት መሆናቸውን በየካ ክፍለ ከተማ በተካሄደው ህዝባዊ ውይይት ላይ የተሳተፉ ነዋሪዎች ተናገሩ።
በአዲስ አበባ በሁሉም ክፍለ ከተሞች "የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግሥት ትሩፋቶች" በሚል ሀሳብ ህዝባዊ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።
በአዲስ አበባ ከተማም ሆነ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተሰሩ ያሉ ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶች የህዝብ እና የመንግስት ቅንጅት ውጤት መሆናቸውን በየካ ክፍለ ከተማ በተካሄደው ህዝባዊ ውይይት የተሳተፉ የህበረተሰብ ክፍሎች ተናግረዋል።

ነዋሪዎቹ ሀገርን የማበልፀግ ርዕይ የሚጨበጥ ውጤት እንዲመዘገብ ማስቻሉንም ጠቅሰዋል።
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ከተማ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ሞገስ ባልቻ በመድረኩ ላይ እንዳሉት በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶች የለውጡ መንግስት የህዝብ ኃብትን በተገቢው መንገድ በመጠቀም የልማት ስራዎችን በፍጥነት እና በጥራት ማከናወን በመቻሉ የመጣ ስኬት ነው ብለዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ ለዘመናት ያልተሰሩ ውዝፍ ስራዎችን በሁሉም ዘርፍ ለመስራት ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።
የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ በበኩላቸው ከተሞችን ለመለወጥ በሚደረገው ጥረት የነዋሪው ሚና ከፍተኛ መሆኑን አንስተዋል።
ኢትዮጵያ በጉባ ብስራቶች ይፋ ያደረገቻቸው ፕሮጀክቶች ሲጠናቀቁ ሀገርን የማበልፀግ ርዕይን እውን እንደሚያደርጉ ያብራሩት ደግሞ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ(ዶ/ር) ናቸው።
በየካ ክፍለ ከተማ ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር በተደረገው ዉይይት ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026