የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ከተማዋን የማልማት ተግባር ባለሀብቱን እና ነዋሪውን ባሳተፈ መልኩ በቅንጅት እየተካሄደ ነው

Dec 8, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 27/2018(ኢዜአ)፦ አዲስ አበባ ከተማን የማልማት እና ምቹ የመኖሪያ ከተማ የማድረጉ ሂደት በዋነኛነት ባለሀብቱን እና ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ በቅንጅት እየተካሄደ መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ በሁሉም ክፍለ ከተሞች ህዝባዊ ውይይት የተካሄደ ሲሆን፤ በአራዳ ክፍለ ከተማም የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) እና የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ በተገኙበት ህዝባዊ መድረኩ ተካሂዷል፡፡


በውይይቱ መክፈቻ ላይ ባለፈው አመት ከተካሄዱ የህዝብ ውይይቶች በኋላ ከነዋሪው ለተነሱ ጥያቄዎች የተሰጡ ምላሾች፣ የከተማ አስተዳደሩ ህዝብን ባሳተፈ መልኩ እያከናወናቸው ያሉ የልማት ስራዎች እና የመጡ ለውጦችን እንዲሁም ያጋጠሙ ተግዳሮቶች፣ እንደሀገርም በኢኮኖሚ፣ በማህባራዊ እና ፖለቲካ የተከናወኑ ተግባራትን እና ቀጣይ አቅጣጫዎችን የተመለከተ ገለጻ ተደርጓል፡፡

የውይይቱ ተሳታፊዎችም ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ በሀገር ደረጃ እና በአዲስ አበባ ከተማ የመጡ ለውጦች የሚደነቁ እና ተጨባጭ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

የውይይቱ ተሳታፊዎች ሊፈቱ ይገባቸዋል ያሏቸውን ጥያቄዎች እና አስተያየቶችም አንስተዋል፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመድረኩ ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ ሲሆን ከተማዋን የማልማት እና ምቹ የመኖሪያ ከተማ የማድረጉ ሂደት በዋነኛነት የግል ባለሀብቱን እና ነዋሪውን ባሳተፈ መልኩ በቅንጅት እየተካሄደ ይገኛል ብለዋል፡፡

ነዋሪዎቹ ያነሷቸው ጥያቄዎች በአብዛኛው ታቅደው በስራ የሚመለሱ መሆናቸውን የገለፁት ደግሞ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) ናቸው።

በቀጣይም በግብርና እና በኢንዱስትሪ ምርትና ምርታማነት ላይ እየተመዘገበ ያለውን ስኬት አጠናክሮ ማስቀጠል ዋነኛው መፍትሄ መሆኑን ተናግረዋል።

የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ በበኩላቸው በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወኑ ስኬታማ የልማት ተግባራትን በሌሎች የሀገሪቱ ከተሞች የማስፋት ስራ በስፋት መከናወኑን ተናግረዋል።

ህዝባዊ ውይይቱ በቀጣይነትም በወረዳ እና በብሎክ ደረጃ እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025