የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ከተማዋን የማልማት ተግባር ባለሀብቱን እና ነዋሪውን ባሳተፈ መልኩ በቅንጅት እየተካሄደ ነው

Dec 8, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 27/2018(ኢዜአ)፦ አዲስ አበባ ከተማን የማልማት እና ምቹ የመኖሪያ ከተማ የማድረጉ ሂደት በዋነኛነት ባለሀብቱን እና ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ በቅንጅት እየተካሄደ መሆኑን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ደረጃ በሁሉም ክፍለ ከተሞች ህዝባዊ ውይይት የተካሄደ ሲሆን፤ በአራዳ ክፍለ ከተማም የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) እና የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ በተገኙበት ህዝባዊ መድረኩ ተካሂዷል፡፡


በውይይቱ መክፈቻ ላይ ባለፈው አመት ከተካሄዱ የህዝብ ውይይቶች በኋላ ከነዋሪው ለተነሱ ጥያቄዎች የተሰጡ ምላሾች፣ የከተማ አስተዳደሩ ህዝብን ባሳተፈ መልኩ እያከናወናቸው ያሉ የልማት ስራዎች እና የመጡ ለውጦችን እንዲሁም ያጋጠሙ ተግዳሮቶች፣ እንደሀገርም በኢኮኖሚ፣ በማህባራዊ እና ፖለቲካ የተከናወኑ ተግባራትን እና ቀጣይ አቅጣጫዎችን የተመለከተ ገለጻ ተደርጓል፡፡

የውይይቱ ተሳታፊዎችም ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ በሀገር ደረጃ እና በአዲስ አበባ ከተማ የመጡ ለውጦች የሚደነቁ እና ተጨባጭ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

የውይይቱ ተሳታፊዎች ሊፈቱ ይገባቸዋል ያሏቸውን ጥያቄዎች እና አስተያየቶችም አንስተዋል፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመድረኩ ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ ሲሆን ከተማዋን የማልማት እና ምቹ የመኖሪያ ከተማ የማድረጉ ሂደት በዋነኛነት የግል ባለሀብቱን እና ነዋሪውን ባሳተፈ መልኩ በቅንጅት እየተካሄደ ይገኛል ብለዋል፡፡

ነዋሪዎቹ ያነሷቸው ጥያቄዎች በአብዛኛው ታቅደው በስራ የሚመለሱ መሆናቸውን የገለፁት ደግሞ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር) ናቸው።

በቀጣይም በግብርና እና በኢንዱስትሪ ምርትና ምርታማነት ላይ እየተመዘገበ ያለውን ስኬት አጠናክሮ ማስቀጠል ዋነኛው መፍትሄ መሆኑን ተናግረዋል።

የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ በበኩላቸው በአዲስ አበባ ከተማ የተከናወኑ ስኬታማ የልማት ተግባራትን በሌሎች የሀገሪቱ ከተሞች የማስፋት ስራ በስፋት መከናወኑን ተናግረዋል።

ህዝባዊ ውይይቱ በቀጣይነትም በወረዳ እና በብሎክ ደረጃ እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026