የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

መፍትሔ አፍላቂ የቴክኖሎጂ ፈጣሪ ወጣቶች

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማኑፋክቸሪንግ ትምህርት ክፍል አሰልጣኝ ወርቁ ፈንታሁን ከጓደኛው ጋር በመሆን በኢትዮጵያ ያለውን የዶሮ እርባታ ስራን ዘመናዊ ማድረግ የሚያስችል ቴክኖሎጂ ፈጥረዋል።

ዘመናዊ የዶሮ ማርቢያ ቤት(ኬጅ) ለመፍጠር ያነሳሳቸው በባህላዊ መንገድ የሚከናወነውን አሰራር ለማዘመን በማሰብ መሆኑን ተናግረዋል።

ዘመናዊው የዶሮ ኬጅ በተወሰነ አካባቢ ላይ በርካታ ዶሮዎችን ለማርባትና ዶሮዎቹን በንጹህ እና ጤንነታቸው በተጠበቀ ቦታ ማርባት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

የሚገኘውን የእንቁላል ምርት ሳይሰበር በቀላሉ መሰብሰብ የሚቻልበትን እድልም ይፈጥራል ብለዋል።

በቀጣይም ቴክኖሎጂው ለዘርፉ ውጤታማነት ከሚኖረው ፋይዳ አንጻር የማስተዋወቅና በስፋት ተመርቶ ወደ ገበያ እንዲቀርብ እንደሚሠሩ ጠቁመዋል።

አካል ጉዳተኞችን በቀላሉ መመገብና ፈሳሽ ነገሮችን ማጠጣት የሚያስችል ሮቦት የሰራው ደግሞ በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የኢንዱስትሪያል ኤሌክትሮኒክስ ቴክኖሎጂ የደረጃ አራት ተመራቂ ተማሪ ዳግም ጋርጠው ነው።


ሮቦቱ ያለምንም የሰው ንክኪ አካል ጉዳተኞች በቀላሉ በሚጠቀሙበት መልኩ የተሠራ ነው ብሏል።

ስራው ውጤታማ እንዲሆን ኮሌጁ የግብዓት፣ የሙያ እና ሌሎች ድጋፎች እንዳደረገለትም ተናግሯል።

በኮሌጁ የቴክኖሎጂ ልማትና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ምክትል ዲን ደሜ መርሻ በአሰልጣኞችና በሰልጣኞች ቅንጅት ውጤታማ የፈጠራ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል።


የመኖ መፍጫ፣ የዘመናዊ ዶሮ ኬጅ እና የፕላስቲክ መፍጫና ማቀነባበሪያ እንዲሁም ፕላስቲኩን ወደ ተለያየ ምርት መቀየር የሚችሉ ማሽኖች በኮሌጁ ተሰርተው ጥቅም ላይ ከዋሉ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውጤቶች መካከል መሆናቸውን አብራርተዋል።

የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን ጥቅም ላይ ለማዋል ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት እየሰራ እንደሚገኝና ፈጠራዎቹን የማስተዋወቅ ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።


የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት ቴክኖሎጂ ፈጣሪ ባለሙያዎችን እንዲሁም ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን እንዲያመነጩ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ የምታስገባቸውን የተለያዩ የቴክኖሎጂ ውጤቶች በሀገር ውስጥ ለመተካት፣ አዳዲስ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን የመፍጠር ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝም ገልፀዋል።

በቴክኒክና ሙያ የሚሰሩ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች በሀገር ልማት ላይ አበረታች ወጤት እያመጡ መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል።

ኢንስቲትዩቱ ሀገራዊ የክህሎት ማበልፀጊያ ፕሮግራም ተግባራዊ በማድረግ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ያላቸውን ዜጎች ውጤታማ እንዲሆኑ ከተለያዩ አካላት ጋር በመሆን እየደገፈ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025