የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

መፍትሔ አፍላቂ የቴክኖሎጂ ፈጣሪ ወጣቶች

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማኑፋክቸሪንግ ትምህርት ክፍል አሰልጣኝ ወርቁ ፈንታሁን ከጓደኛው ጋር በመሆን በኢትዮጵያ ያለውን የዶሮ እርባታ ስራን ዘመናዊ ማድረግ የሚያስችል ቴክኖሎጂ ፈጥረዋል።

ዘመናዊ የዶሮ ማርቢያ ቤት(ኬጅ) ለመፍጠር ያነሳሳቸው በባህላዊ መንገድ የሚከናወነውን አሰራር ለማዘመን በማሰብ መሆኑን ተናግረዋል።

ዘመናዊው የዶሮ ኬጅ በተወሰነ አካባቢ ላይ በርካታ ዶሮዎችን ለማርባትና ዶሮዎቹን በንጹህ እና ጤንነታቸው በተጠበቀ ቦታ ማርባት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

የሚገኘውን የእንቁላል ምርት ሳይሰበር በቀላሉ መሰብሰብ የሚቻልበትን እድልም ይፈጥራል ብለዋል።

በቀጣይም ቴክኖሎጂው ለዘርፉ ውጤታማነት ከሚኖረው ፋይዳ አንጻር የማስተዋወቅና በስፋት ተመርቶ ወደ ገበያ እንዲቀርብ እንደሚሠሩ ጠቁመዋል።

አካል ጉዳተኞችን በቀላሉ መመገብና ፈሳሽ ነገሮችን ማጠጣት የሚያስችል ሮቦት የሰራው ደግሞ በጀነራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የኢንዱስትሪያል ኤሌክትሮኒክስ ቴክኖሎጂ የደረጃ አራት ተመራቂ ተማሪ ዳግም ጋርጠው ነው።


ሮቦቱ ያለምንም የሰው ንክኪ አካል ጉዳተኞች በቀላሉ በሚጠቀሙበት መልኩ የተሠራ ነው ብሏል።

ስራው ውጤታማ እንዲሆን ኮሌጁ የግብዓት፣ የሙያ እና ሌሎች ድጋፎች እንዳደረገለትም ተናግሯል።

በኮሌጁ የቴክኖሎጂ ልማትና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ምክትል ዲን ደሜ መርሻ በአሰልጣኞችና በሰልጣኞች ቅንጅት ውጤታማ የፈጠራ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል።


የመኖ መፍጫ፣ የዘመናዊ ዶሮ ኬጅ እና የፕላስቲክ መፍጫና ማቀነባበሪያ እንዲሁም ፕላስቲኩን ወደ ተለያየ ምርት መቀየር የሚችሉ ማሽኖች በኮሌጁ ተሰርተው ጥቅም ላይ ከዋሉ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውጤቶች መካከል መሆናቸውን አብራርተዋል።

የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን ጥቅም ላይ ለማዋል ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት እየሰራ እንደሚገኝና ፈጠራዎቹን የማስተዋወቅ ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።


የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ተቋማት ቴክኖሎጂ ፈጣሪ ባለሙያዎችን እንዲሁም ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን እንዲያመነጩ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ የምታስገባቸውን የተለያዩ የቴክኖሎጂ ውጤቶች በሀገር ውስጥ ለመተካት፣ አዳዲስ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎችን የመፍጠር ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝም ገልፀዋል።

በቴክኒክና ሙያ የሚሰሩ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች በሀገር ልማት ላይ አበረታች ወጤት እያመጡ መሆኑንም ጨምረው ተናግረዋል።

ኢንስቲትዩቱ ሀገራዊ የክህሎት ማበልፀጊያ ፕሮግራም ተግባራዊ በማድረግ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ያላቸውን ዜጎች ውጤታማ እንዲሆኑ ከተለያዩ አካላት ጋር በመሆን እየደገፈ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026